query_id
stringlengths 32
32
| passage_id
stringlengths 32
32
| query
stringlengths 2
182
| passage
stringlengths 137
1.88k
| label
int64 0
1
|
---|---|---|---|---|
1a30506ca37088923a2db097c5b13afe | d1f62f5c4905dec6211a2bef18eb4dca | በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ተጨማሪ 3 ሰዎች መገኘታቸውን የጤና ሚኒስቴር ገለፀ | አዲስ አበባ፣ የካቲት 16፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በኩዌት፣ ባህሬን እና አፍጋኒስታን በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ተገኝተዋል።መነሻውን ከወደ ቻይና ውሃን ግዛት ያደረገው የኖቭል ኮሮና ቫይረስ ከቻይና ውጭ በርካታ ሃገራትን እያዳረሰ ነው።በዚህም በኩዌት ሶስት እንዲሁም በባህሬን እና አፍጋኒስታን በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች መገኘታቸውን የየሃገራቱ የጤና ሚኒስቴሮች አስታውቀዋል።በትናንትናው እለትም በቻይና 150 እንዲሁም በደቡብ ኮሪያ 70 አዲስ በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች መገኘታቸው ተገልጿል። በኢራን 43 ሰዎች በቫይረሱ የተያዙ ሲሆን እስካሁን 12 ሰዎች ለህልፈት ተዳርገዋል።ይህን ተከትሎም ቱርክ፣ ፓኪስታን እና አርሜኒያ ከኢራን ጋር የሚያዋስናቸውን ድንበር ዘግተዋል፤ አፍጋኒስታንም የጉዞ እገዳ ጥላለች።በጣሊያን ወደ 150 የሚጠጉ ሰዎች በቫይረሱ የተያዙ ሲሆን፥ አራት ሰዎች ለህልፈት መዳረጋቸውም ተገልጿል።የኮሮና ቫይረስ እስካሁን ዓለም ላይ ከ2 ሺህ 600 በላይ ሰዎችን ለህልፈት ሲዳርግ የስርጭት አድማሱም እየተስፋፋ ይገኛል።ምንጭ፡-አልጀዚራትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!
https://t.me/fanatelevision | 0 |
c2eedfa736b983f958b9e5ae48d552fc | c2eedfa736b983f958b9e5ae48d552fc | የዳውሮ ዞን ነዋሪዎች የህወሃት ቡድን የፈጸመውን ጥቃት በማውገዝ ሠልፍ እያካሄዱ ነው | አዲስ አበባ ፣ህዳር 10 ፣2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የዳውሮ ዞን ነዋሪዎች የሕወሓት ቡድን የፈጸመውን ጥቃትና የሀገር ክህደት በመውገዝ በተርጫ ከተማ ሠላማዊ ሠልፍ እያካሄዱ ነው።በሰልፉ ከዳውሮ ዞን አስር ወረዳዎችና ከተርጫ ከተማ የተውጣጡ ነዋሪዎች በመሳተፍ ላይ ይገኛሉ።ሰልፈኞቹ መንግስት በጽንፈኛው ሕወሓት ቡድን ላይ እየወሰደ ያለውን ህግ የማስከበር ዘመቻ እንደሚደግፉ እየገለጹ ነው፡፡እንዲሁም “አረመኔው የጥፋት ቡድን ሀገር ለማፍረስ የሚንቀሳቀስ ጠላት በመሆኑ ከመንግስት ጎን በመሰለፍ እንታገላለን” ሲሉ ያረጋገጡት ሰልፈኞቹ፤ በሀገር መከላከያ ሠራዊት ላይ ቡድኑ ያደረሰውን ጥቃት እንደሚያወግዙ የሚገልጹ መፈክሮችን በማሰማት ላይ ናቸው።በመርሃ ግብሩ ከመከላከያ ሚኒስቴርና ደቡብ ክልል የተውጣጡ አመራሮችም ተገኝተዋል።ሰልፈኞቹ ለሀገር መከላከያ ያላቸውን አጋርነት ለመግለፅ የእርድ እንስሳት ድጋፍና ደም ልገሳ እንደሚካሄድም ኢዜአ ዘግቧል፡፡ | 1 |
7167f5f2e448b5981102f1eec034294b | 32abe8c96e1755d01a61260606468e85 | አስናቀ ሞገስ ዳግመኛ ወደ ባህር ዳር ከተማ አምርቷል | አሰልጣኝ አሸናፊ በቀለን ከቀጠረ በኋላ ወደ ዝውውር ገበያው የገባው አዳማ አራተኛ ተጫዋቹን ሲያስፈርም የአራት ነባር ተጫዋቾችን ውል አራዝሟል፡፡በ2009 የውድድር ዘመን ጅማሮ ኢትዮጵያ መድንን በመልቀቅ ወደ ድሬዳዋ ያመራው አጥቂው ሐብታሙ ወልዴ በቆይታው ወሳኝ ጎሎችን ለቡድኑ ያስቆጠረ ሲሆን ከአማኑኤል ጎበና፣ አስናቀ ሞገስ እና ታሪክ ጌትነት በመቀጠል አራተኛው የአዳማ አዲስ ተጫዋች ሆኗል። ዳዋ ሆቴሳን በጉዳት ባጣባቸው ወቅቶች ሲቸገር የታየው የቡድኑ የአጥቂ መስመርን እንደሚያጠናክርም ይጠበቃል።አዳማ ከተማ ከአዳዲስ ተጫዋቾች በተጨማሪ ነባሮቹን ውል ማደስ ጀምሯል፡፡ በዚህም መሠረት አምበሉ እና የግራ መርመር ተከላካዩ ሱሌይማን መሐመድ፣ የመሐል ተከላካዩ ተስፋዬ በቀለ እንዲሁም አማካዮቹ አዲስ ህንፃ እና ኤፍሬም ዘካሪያስ በአንድ ዓመት ተጨማሪ ውል በአዳማ ቆይታ ያደርጋሉ፡፡ | 0 |
6621880b77ce2915b43f1edf8ecae9bb | 2671f5d2eaa512d7e08d9810207cae0a | በአለም የኮሮናቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 25 ሚሊየንን አለፈ | አዲስ አበባ፣ ሚያዚያ 22፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ ባለፉት በ24 ሰዓታት ውስጥ ለ1 ሺህ 408 ሰዎች የኮሮናቫይረስ ምርመራ መደረጉን የጤና ሚኒስትር ዶክተር ሊያ ታደሰ ገለፁ።ባለፉት በ24 ሰዓታት ውስጥ በተደረገ ምርመራም ተጨማሪ 1 ሰው ላይ የኮሮና ቫይረስ መገኘቱንም ሚኒስትሯ አስታውቀዋል።ቫይረሱ የተገኘባቸው ግለሰብ ኢትዮጵያዊ ሴት ሲሆኑ፥ ነዋሪነታቸው በባህር ዳር ከተማ መሆኑን እና በበሽታው ከተያዘ ሰው ጋር ግንኙነት ያላቸው እንደሆነም ገልፀዋል።ይህንን ተከትሎም በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 131 መድረሱንም ነው ዶክተር ሊያ ያስታወቁት።ዶክተር ሊያ አክለውም በ24 ሰዓት ውስጥ ተጨማሪ አንድ ሰው ከቫይረሱ ማገገሙን አስታውቀው፤ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ከቫይረሱ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 59 መድረሱንም ገልፀዋል።በአጠቃላይ በኢትዮጵያ የኮሮናቫይረስ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 131 ሲሆን፥ ከእነዚህም ውስጥ 67 ሰዎች በለይቶ ህክምና ላይ፤ 59 ሰዎች ደግሞ ከቫይረሱ አገግመዋል።በቫይረሱ የ3 ሰዎች ህይወት ማለፉ የሚታወስ ሲሆን፥ ሁለት ሰዎች ደግሞ ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ መደረጉ አይዘነጋም።የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ። | 0 |
1fe7d7869de75ce18d6b56ae5ac5ab40 | 1fe7d7869de75ce18d6b56ae5ac5ab40 | ከፍተኛ ሊግ | የደሴ ከተማ ተጫዋቾች ላቀረቡት ቅሬታ ክለቡ ምላሽ እንዲሰጠው ፌዴሬሽኑ ጠየቀ | ፌዴሬሽኑ ደሴ ከተማ ቀሪ የውል ዓመት ያላቸው አራት ተጫዋቾችን ስለመልቀቁ በአስር ቀን ውስጥ ማብራርያ እንዲሰጠው አሳስቧል፡፡ በከፍተኛ ሊጉ ተሳታፊ በሆነው ደሴ ከተማ ዐምና ይጫወቱ የነበሩ አራት ተጫዋቾች ማለትም ሚሊዮን በየነ፣ ኃይለማሪያም እሸቱ፣ ዓለማየሁ ማሞ እና ሊቁ አልታዬ ዘንድሮ በክለቡ የሚያቆያቸው የሰባት እና የስድስት ወራት የውል ቆይታ እያላቸው ክለቡ ግን ተጫዋቾቹን ከስብስቡ ውጪ ማድረጋቸውን ተጫዋቾቹ ለሦስት ጊዜያት ለፌዴሬሽኑ ባስገቡት ደብዳቤ አቤቱታቸውን አሰምተዋል።በዚህም መሠረት የፌዴሬሽኑ የዲሲፕሊን ኮሚቴ ተጫዋቾቹ የውል ጊዜ እያላቸው ከክለቡ መሰናበታቸውን በመግለፅ “ክለቡ በአስር ቀናት ውስጥ አፋጣኝ ምላሽ ይስጠኝ” ሲል አሳስቧል፡፡ | 1 |
c62000a7807ffeae75f5bf736213dae3 | 589a56df917775acf1bc1b15ae5bfa61 | ኢትዮጵያ በሴካፋ አትሳተፍም | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን በሴካፋ የመጨረሻ የምድብ ጨዋታ ነገ ዩጋንዳን ለመግጠም እየተዘጋጀች ባለበት ወቅት አስገራሚ መረጃ ከወደ ኬንያ ተሰምቷል።በኬንያ አዘጋጅነት እየተካሄደ በሚገኘው የሴካፋ ዋንጫ ላይ እየተሳተፈ የሚገኘው የኢትዮዽያ ብሔራዊ ቡድን በመጀመርያ የምድብ ጨዋታው ደቡብ ሱዳንን 3-0 በሆነ ውጤት በማሸነፍ አጀማመሩን ቢያሳምርም በሴካፋ የተሳትፎ ታሪኩ ተሸንፎ በማያቀው ውጤት በቡሩንዲ 4-1 ተረትቶ ወደ ግማሽ ፍፃሜ የመግባት እድሉን አጥብቧል።ብሔራዊ ቡድኑ ወደ ግማሽ ፍፃሜው ለማለፍ ነገ የዩጋንዳ ብሔራዊ ቡድንን የማሸነፍ ብቻ ግዴታ ውስጥ መግባቱን ተከትሎ በቡድኑ ላይ ያለው በራስ መተማመን የወረደ ይመስላል። ከኬንያ ለቡድኑ ቅርበት ካላቸው ምንጮች እንዳረጋገጥነው ከሆነ ዩጋንዳን ማሸነፍ ከባድ እንደሆነ በማሰብ የቡድኑ አባላት ሰኞ ወደ አአ የሚመጡበት የአውሮፕላን ትኬት እንዲላክላቸው ለኢትዮጵያ እግርኳስ ፌዴሬሽን ጥያቄ ጠይቀዋል። ፌዴሬሽኑም የአውሮፕላን ትኬቱን ለመላክ እንቅስቃሴ መጀመሩ ተሰምቷል።የሴካፋ ውድድር ላይ ብሔራዊ ቡድኑ የመሳተፉ ጉዳይ ብዙ በማያሳምንበት እና ከባድ ሽንፈት ባስተናገደበት ወቅት እንዲህ ያለ መረጃ መውጣቱ አስገራሚ ሆኗል። | 0 |
7588f9125c55576841d361e2b0cb18d9 | bf81125ed0e7fff5ed05fdb68fae01ff | የነዳጅ እጥረት በደሴ | በደሴ ከተማ የሚገኙ የሙስሊሙ ማኅበረሰብ አባላት በእምነት ተቋማት ላይ የደረሰውን ጥቃት አወገዙ፡፡በደሴ ከተማ አስተዳደር ከሙስሊሙ ማኅበረሰብ ክፍሎች የተወጣጡ የእምነቱ ተከታዮች በሞጣ ከተማ በእምነት ተቋማት ላይ ደረሰው ጥቃት አሳፋሪ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የእምነቱ ተከታዮች በደሴ ከተማ በሚገኘው ዐረብ ገንዳ መስጂድ ባደረጉት ውይይት አጥፊዎቹ በሕግ ሊጠየቁ እንደሚገባም ጠይቀዋል፡፡ጥቃቱ ከመድረሱ በፊትም ሆነ ከደረሰ በኋላ መንግሥት እያሳዬ ያለው ለዘብተኛ አቋም መታረም እንደሚገባውም አሳስበዋል፡፡ የክልሉ መንግሥት በመስጂዶች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት እንደሚደርስ መረጃዎች እንደነበሩት በማንሳትም ቅድመ መከላከል አልሠራም በሚል ወቅሰዋል፡፡ ድርጊቱ ከተፈጸመ በኋላም በቁጥጥር ሥር ያዋላቸው ተጠርጣሪዎች ቁጥር አነስተኛ እንደሆነ ገልጸዋል፡፡ መንግሥት የተቃጠሉ ቤተ እምነቶችን እንዲሠራና የተዘረፉ ንብረቶችን እንዲመለሱ ማድረግ እንደለበትም ተናግረዋል፡፡ችግሩ እንዲባባስም ሆነ የቤተ እምነቶች እንዲቃጠሉ የሚዲያ አካላት ድርሻ ከፍተኛ እንደሆነም ነው ተወያዮቹ ያነሱት፡፡ የሚዲያ አውታሮች በተለይ በመስጂዶች ላይ ጥቃት ሲደርስ የሚሰጡት ሽፋን ሚዛናዊ እንዳልሆና መታረም እንደሚገባውም መክረዋል፡፡ መንግሥት የተቃጠሉ ቤተ እምነቶችን እንዲሠራና የተዘረፉ ንብረቶችን እንዲያስመልስም አሳስበዋል፡፡ዘጋቢ፡- ተመስገን አሰፋአዘጋጅ፡- ኃይሉ ማሞ | 0 |
ae0df79fae4ae52a92a79e1f60810105 | f3ab0f4e7230fb4d0507b50dcaec36c4 | ባለፉት 24 ሰአት ውስጥ 15 ሰዎች የካሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው ተገለፀ | አዲስ አበባ፣ ሐምሌ 10፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰአታት ለ7 ሺህ 407 ሰዎች የላቦራቶሪ ምርመራ ተደርጎ 344 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡ከዚህ ባለፈም ባለፉት 24 ሰአታት ውስጥ 13 ሰዎች ህይወታቸው ያለፈ ሲሆን ከዚህ ውስጥ አራቱ የህክምና እርዳታ ሲደረግላቸው የቆዩ እንዲሁም ዘጠኙ ከአስከሬን ላይ በተደረገ ምርመራ ቫይረሱ የተገኘባቸው ናቸው፡፡አሁን ላይም በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ ሳቢያ ለህልፈት የተዳረጉ ሰዎች ቁጥር 163 መድረሱንም ሚኒስቴሩ አስታውቋል፡፡በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥርም 9 ሺህ 147 ደርሷል፡፡በትናንትናው እለት 86 ሰዎች ያገገሙ ሲሆን ይህን ተከትሎም ከቫይረሱ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 4 ሺህ 900 ሆኗል፡፡ | 0 |
9ffd4cb268607166b26bc41e93924cda | 6c4f5651c65e8c389d774a6442a9329b | የ114 የእድሜ ባለፀጋ ከኮሮና ቫይረስ ሙሉ በሙሉ አገግመው ከኤካ ኮተቤ ሆስፒታል ወጡ | ርእሰ መሥተዳድሩ የቦሩ ሜዳ ሆስፒታል የኮሮና ቫይረስ ሕክምና መስጫ ማዕከልን ጎብኝተዋል።ባሕር ዳር፡ ሚያዝያ 30/2012 ዓ.ም (አብመድ) በኢትዮጵያ የኮሮና ቫይረስ መከሰቱ ከተረጋገጠ ወዲህ በመንግሥትና በሕዝቡ የመከላከል ርምጃዎች እየተወሰዱ ነው። ለኮሮና ቫይረስ ተጠቂዎችን ሕክምና ለመስጠት የሚያስችሉ ማዕከላትን ማዘጋጀት ደግሞ አንዱ ዐብይ ተግባር ነው።ለደቡብ ወሎና ደሴ ከተማ የኮሮና ቫይረስ ሕክምና ለመስጠት የቦሩ ሜዳ ሆስፒታል በማዕከልነት ተመርጦ ቁሳቁሶችን እያሟላ ይገኛል።የሆስፒታሉ ሥራ አስኪያጅ አቶ ሲሳይ ተበጀ እንዳሉት ደረጃቸውን የጠበቁ 100 አልጋዎች ከነአጋዥ ቁሳቁሶች ተዘጋጅተዋል ብለዋል። በአካባቢው የከፋ ችግር ቢያጋጥም እስከ 1ሺህ አልጋዎችን ማሳረፍ የሚችል ቦታ መኖሩንም ነው የተናገሩት።ሆስፒታሉ የተሟላ የሕክምና አገልግሎት እንዲሰጥ የጽኑ ሕሙማን ማከሚያ መሣሪያና የባለሙያዎች አልባሳት እንዲሟላላቸውም ጠይቀዋል። | 0 |
a8833eb71cc6878e6423479811bfec86 | a8833eb71cc6878e6423479811bfec86 | የቱርክ ባልሥልጣን ስለኻሾግዢ ከተመድ የፍርድ ጠቢብ ጋር ተወያዩ | የቱርክ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር የሳዑዲ ተወልጅ ጋዜጠኛ ዣማል ኻሾግዢ አገዳደልን አስመልክቶ ከሚመረምረው የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የፍርድ ጠቢብ ጋር ዛሬ ተገናኝተው ተነጋገረዋል። ቱርክ ዓለምቀፍ ምርመራ እንዲካሄድበት እየጠየቀች ነው።የመንግሥታቱ ድርጅት ልዩ መርማሪ አጀንስ ካላማንደር እስከ ቅዳሜ ድረስ ቱርክ በመቆየት የኢስታምቡል ዋና ዐቃቤ ህግ ከሚገኑባቸው ባለሥልጣኖች ጋር ተገናኝተው ይነጋገራሉ።አጀንስ ካላማንደር ቱርክ ካሉት የሳዑዲ አረብያ አምባሳደር ጋር ለመነጋገርና ምርመራውን ለማካሄድ ሳዑዲ አረብያም ጭምር ለመሄድ ላቀረቡት ጥያቄ የሳዑዲ አረብያ ባለሥልጣኖች ምላሽ ሰጥተው እንዳሆነ ማራጋገጫ አልሰጡም። | 1 |
3742fcb886a2cc566485c20a71c409a4 | 3742fcb886a2cc566485c20a71c409a4 | በኢትዮጵያ አጠቃላይ 50 ሰዎች ከኮሮና በሽታ አገግመዋል፡፡ | በኢትዮጵያ ባለፉት 24 ሰዓታት ለ943 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ የላቦራቶሪ ምርማራ ተደርጓል፤ በአንድ ሰው ላይም ቫይረሱ መገኘቱ ተረጋግጧል፡፡ የጤና ሚኒስቴር በማኅበራዊ ገጹ እንዳስታወቀው ቫይረሱ የተገኘባቸው ትውልደ ኢትዮጵያዊ እንግሊዛዊ የ45 ዓመት ጎልማሳ ናቸው፤ ከእንግሊዝ ተመልሰው በለይቶ ማቆያ የነበሩ እንደሆነም ነው የተገለጸው፡፡ባለፉት 24 ሰዓታት በኢትዮጵያ ተጨማሪ 9 ሰዎች ከኮሮና በሽታ ማገገማቸውም ተነግሯል፤ ስምንቱ ከአዲስ አበባና አንዱ ከባሕር ዳር መሆናቸውም ተመላክቷል፡፡ በዚህም በኢትዮጵያ ከኮሮና ቫይረስ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 50 ደርሷል፡፡ 69 ሰዎች ደግሞ በሕክምና ክትትል ላይ ይገኛሉ፡፡የጤና ሚኒስቴር ኅብረተሰቡ አሁንም ጥንቃቄውን እንዲያጠናክር አሳስቧል፡፡ አካላዊ ርቀትን መጠበቅ፣ እንጅን አዘውትሮ በውኃና ሳሙና መታጠብ፣ የፊት መሸፈኛ መጠቀም ተጠናክሮ እንዲቀጥልም አሳስቧል፡፡ | 1 |
6964be04508bcaf1a2e8feee7dca71ac | ae4bf97664eb31d3c045a57fa4062fe3 | መንግሥት የሰጠውን የ72 ሰዓት ጊዜ በመጠቀም በርካታ የትግራይ ሚሊሻና ልዩ ኃይል አባላት እጅ እየሰጡ ነው | አዲስ አበባ፣ ህዳር 7፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የህወሓት ቡድን ያሰማራቸው ልዩ ኃይሎችን በመደምሰስ በሺዎች የሚቆጠሩ ለውጊያ ሲጠቀምባቸው የነበሩ የጦር መሳሪያዎች በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡የታጣቂው ህወሓት ልዩ ኃይል በሀገር መከላከያ ሰራዊት፣በአማራ ልዩ ኃይልና በሚሊሻ አባላት እየተደመሰሰ ይገኛል።በዚህ ታላቅ ጀብድ ሰራዊቱ የህወሓት ስግብግብ ኃይል ለጦርነት እየተጠቀመባቸው የነበሩ ከ230 በላይ ክላሽንኮቭ፣ ከ1 ሺህ በላይ የእጅ ቦምብና ሌሎች ተተኳሽ መሳሪያዎችን በቁጥጥር ስር ማዋሉን የደቡብ ዕዝ የሰው ሐብት ልማትና የሚዲያ አስተባባሪ ኮሎኔል ደጀኔ ጸጋዬ ተናግረዋል።እየተካሄደ ባለው ህግ የማስከበር ለህልውና ዘመቻ የአማራ ልዩ ኃይልና የሚሊሻ አባላት በተሰጣቸው ቀጣና በጠላት ላይ ከባድ ወታደራዊ ጥቃት በመፈጸምና በመደምስስ ግዳጃቸውን በብቃት እየፈጸሙ መሆኑንም አመላክተዋል።የመከላከያ ሰራዊት፣ የአማራ ልዩ ኃይልና የሚሊሻ አባላት በትህነግ አፋኙ ቡድን ላይ እያከናወኑት ባለው ህግ የማስከበር ለህልውና ዘመቻ የአካባቢው ህዝብ የምግብና ሌሎች ድጋፎችን እያደረገ መሆኑንም አብመድ ዘግቧል።በሌላ በኩል የትምዕት አንዱ ቅርጫፍ የሆነው የሱር ኮንስትራክሽን ድርጅት ውስጥ በቃፍታ ሁመራ በርካታ የጦር መሳሪያ መያዙ ነው የተገለጸው።የሱር ኮንስትራክሽን ድርጅት ከባእከር ቃፍታ አዲረመጽ የመንገድ ስራ ተረክቦ የገነባው ካምፕ በአማራ ልዩ ኃይል ሲፈተሽ የተለያዩ የጦር መሳሪያዎች ተገኝተዋል።የአማራ ልዩ ኃይል የዘመቻ ኃላፊ ኮማንደር ምስጋናው ተሰማ እንደተናገሩት፣ የኮንስትራክሽን ድርጅቱ መንገድ እገነባለሁ በማለት የጦር መሳሪያ በማከማቸት የህወኃት የጦር አጋዥ በመሆን ሲሰራ እንደነበር በካምፑ ፍተሻ ስናደርግ ያገኘነው ጦር መሳሪያ ማሳያ ነው ሲሉ ተናግረዋል። | 0 |
081b381ee0f36267938f8cf475aac5b0 | fcd5e0dad1f4e3df8a4d06215c0ba640 | የጊኒ ፕረዚዳንታዊ ምርጫ | የኢትዮጵያ ከ20 አመት በታች ሴቶች ብሄራዊ ቡድን ከቡርኪና ፋሶ ጋር በኦጋዱጉ በቀጣይ ቅዳሜ የሚያደርገው የጠአለም ከ20 አመት በታች ሴቶች ማጣርያ ጨዋታ በሃገሪቱ ባለው አለመረጋጋት ምክንያት በቡርኪና ፋሶ የመካሄዱ ጉዳይ አጠራጣሪ ሆኗል፡፡ለ27 አመት ስልጣን ላይ ቆይተው ባለፈው አመት ከስልጣን የተወገዱት ብሌስ ኮምፓሬ ታማኝ እንደሆነ የሚነገርለት በጄኔራል ጂልበርት ዴንዴሬ የሚመራ የቡርኪናፋሶ የጦር ኃይል ባለፈው ሐሙስ በሽግግር መንግስቱ ላይ መፈንቅለ መንግስት ማካሄዱንና ሃገሪቱን መቆጣጠሩን በብሄራዊ ቴሌቪዥን ማወጁን ተከትሎ በሃገሪቱ አለመረጋጋት ሰፍኗል፡፡ ከ3 ሳምንት በኋላ ሃገራዊ ምርጫ ልታደርግ አቅዳ የነበረችው ሃገርም በትርምስ ውስጥ ትገኛለች፡፡ በጎዳናዎች ላይ ከፍተኛ ነውጥም እያስተናገደች ትገኛለች፡፡ይህንን ተከትሎ የኢትዮጵያ ከ20 አመት በታች ሴቶች ብሄራዊ ቡድን ሌሎች አማራጮችን ለመመልከት ለካፍ ጥያቄ እንዳቀረበ የፌዴሬሽኑ ህዝብ ግንኙነት አቶ ወንድምኩን አላዩ ለሶከር ኢትዮጵያ ተናግረዋል፡፡‹‹ ስለ መፈንቅለ መንግስቱ መረጃው ደርሶናል፡፡ ወደ ቡርኪናፋሶ የሚደረጉ በረራዎችም ተቋርጠዋል፡፡ ወደፊት መሆን ስለሚገባው ነገር ለካፍ ጥያቄ አቅርበናል፡፡ ውሳኔውንም እየጠበቅን ነው›› ብለዋል፡፡የካፍ ምላሽ በፍጥነት የሚታወቅ ከሆነ የኢትዮጵያ ከ20 አመት በታች ሴቶች ብሄራዊ ቡድን ከቡርኪና ፋሶ አቻው ጋር የሚያደርገው ጨዋታ በጎረቤት ሃገራት ሊካሄድ ይችላል፡፡ከ12 አመታት በፊት የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ለቱኒዚያ የ2004 የአፍሪካ ዋንጫ ለማለፍ ወርቃማ እድል የነበረው ቢሆንም በመፈንቅለ መንግስት ትርምስ ስትታመስ ከነበረችው ላይቤርያ ጋር በሞኖሮቪያ ተጫውታ 1-0 ተሸንፋለች፡፡ በአንፃሩ የጊኒ ብሄራዊ ቡድን ከላይቤርያ ጋር የምታደርገውን ጨዋታ በጎረቤት ሃገር ጋና እንዲደረግ ለካፍ ጥያቄ በማቅረብ በገለልተኛ ሜዳ አሸንፋ ማለፏ የሚታወስ ነው፡፡ | 0 |
671a306c8eb0e86b7dcb07bb854dad35 | 671a306c8eb0e86b7dcb07bb854dad35 | በዓለም አቀፍ አቅራቢዎች በጨረታ ይፈፀም የነበረውን የስንዴ አቅርቦት ለመቀየር እየተሰራ ነው | አዲስ አበባ ፣ ጥር 7፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የመንግስት የግዥና ንብረት አስተዳደር አገልግሎት ኤጀንሲ በዓለም አቀፍ አቅራቢዎች በጨረታ ይፈፀም የነበረውን የስንዴ አቅርቦት ለመቀየር እየሰራ መሆኑን አስታወቀ።የአቅርቦት ሂደቱን ለማፋጠን የመንግስት ለመንግስት ግብይትን ተግባራዊ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን፥ የኤጀንሲው ዋና ዳይሬክተር ወይዘሮ ፅዋዬ ሙሉነህ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል።የግብይቱ ተግባራዊ መሆን ሀገሪቱ ላይ ከዚህ ቀደም በደላሎችና በነጋዴዎች ይደርስ የነበረውን ኢኮኖሚያዊ ኪሳራ በመታደግ፥ ከጨረታ ጋር ታያይዞ የሚጠፋውን ጊዜ እና የንብረት ብክነት ለመቆጣጠር ያስችላልም ነው ያሉት።ይህን የግብይት ሂደት እውን ለማድረግ በገንዘብ ሚኒስቴር የሚመራ ቡድን የተቋቋመ ሲሆን፥ ቡድኑ በዩክሬን፣ ሩሲያ እና አውስትራሊያ የስንዴ ጥራት፣ መጠን እና አይነትን በተመለከተ ምልከታ አድርጓል ብለዋል።ዳይሬክተሯ አያይዘውም ለተለያዩ ሴክተር መስሪያ ቤቶች የታዘዘው ስንዴ ወደ ሃገር ውስጥ እየገባ መሆኑን ጠቅሰዋል።ከዚህ ውስጥ ለኢትዮጵያ ንግድ ስራ ኮርፖሬሽን 400 ሺህ ሜትሪክ ቶን፣ ለብሄራዊ አደጋ ስጋት ስራ አመራር ኮሚሽን 200 ሺህ ሜትሪክ ቶን፣ በግብርና ሚኒስቴር የሚገዛ 155 ሺህ ሜትሪክ ቶን ስንዴ በግዥ ሂደት ላይ እንደሚገኝም አንስተዋል።ከዚህ ውስጥ ለኢትዮጵያ ንግድ ስራ ኮርፖሬሽን የታዘዘው ስንዴ የተወሰነው ወደ ሃገር ውስጥ እየገባ መሆኑንም አውስተዋል።በተያያዘም ኤጀንሲው ከተወገዱ ተሽከርካሪዎች፣ የተቋማት የተለያዩ ንብረቶች እና ቁርጥራጭ ብረቶች 32 ሚሊየን 669 ሺህ 809 ብር ከ97 ሳንቲም ማግኘቱንም ገልጸዋል።ኤጀንሲው የሚሰጣቸውን አገልግሎቶች ምቹ እና ቀልጣፋ ለማድረግ የሚያስችል አሰራር እየዘረጋ መሆኑን ያነሱት ዳይሬክተሯ፥ የውስጥ ችግሮችን የመለየት፣ አደጃጀትን የማዘመን፣ ከባለድርሻ አካላት ጋር ያለውን ትብብርና ቅንጅት ማሳደግን ጨምሮ የህግ ማዕቀፎችን የማሻሻል ስራ እየሰራ መሆኑን አስረድተዋል።ኢትዮጵያ ከአመታዊ በጀቷ ከ65 እስከ 70 በመቶ የሚሆነው እና ከሃገር ውስጥ አጠቃላይ ምርት 15 በመቶውን ለግዥ እንደምታውል መረጃዎች ያመላክታሉ።በሙሃመድ አሊ | 1 |
33d471c5672f129b8c17063cf8185471 | 23a736a321d6d657982bbcc53ff72cf9 | ለኢትዮጵያ ወጣቶች አካዳሚ 62 ታዳጊዎች ተመለምለዋል | የባርሴሎናው ላሜሲያ ወጣቶች አካዳሚ የግብ ጠባቂ ዋና አሰልጣኝ የሆነው ሪቻርድ አርጋይ በሀገራችን ኢትዮጵያ ላሉ የግብ ጠባቂ አሰልጣኞች ትናንት ምሽት ስልጠና ሰጥቷል፡፡የካፍ ኤሊት ኢንስትራክተር አብርሀም መብራቱ እና የአሜሪካው ሳክሪሜንቶ የእግር ኳስ አካዳሚ አሰልጣኝ አምሳሉ ፋንታሁን በጋራ ሆነው ከተለያዩ አለማት ካሉ የእግርኳስ ባለሙያዎች ጋር ግንኙነት በመፍጠር በተለያዩ ጊዜያት የሚሰጠው የኦንላይን ስልጠና ቀጥሎ ትናንት ምሽት 4፡00 ጀምሮ ከሁለት ሰአታት በላይ የቆየ ስልጠና ተሰጥቷል፡፡ በስፔኑ ሀያል ክለብ ባርሴሎና ውስጥ በሚገኘው የላሜሲያ ወጣት ቡድን የግብ ጠባቂ ዋና አሰልጣኝ በመሆን እየሰራ የሚገኘው ሪቻርድ አርጋይ በዋናነት ይህን ስልጠና የሰጠ ሲሆን በስፔን ከፍተኛ የስፖርት ኤክስፐርት ዴቪድ ሮበርትሰን በጋራ በመሆን አቅርበዋል፡፡ሪቻርድ በተለይ ስለ ባርሴሎና አካዳሚ የግብ ጠባቂዎች የስልጠና መንገድ እና ሒደት በአሜሪካ እና ካናዳ ሰጥተውት የነበረውን ስልጠና ወደ ሀገራችን ኢትዮጵያ በማምጣት ነው በZOOM ታግዘው ለሀገራችን ግብ ጠባቂ አሰልጣኞች ያጋሩት። በስልጠናው በተለየ መልኩ ባርሴሎና ከ13 ዓመት ጀምሮ ከላሜሲያ አካዳሚ እስከ ዋናው ቡድን የሚከተላቸውን የተግባር፣ የክፍል እንዲሁም መሰል የስልጠና ሒደቶችን በዝርዝር አቅርበዋል፡፡ ግብ ጠባቂዎች ሊተገብሯቸው የሚገቡ መሠረታዊ የቴክኒክ ጉዳዮችን በማንሳትም ገለፃ አድርገዋል። ከዚህም ባለፈ የባርሴሎናው ላሜሲያ አካዳሚ ውስጥ ያሉ ወጣቶች የመጡበት መንገድ እና ጀርመናዊው የአሁኑ የባርሴሎና ቋሚ ግብ ጠባቂ አንድሬ ቴር ስቴገን የሚከተላቸው የጨዋታ መንገዶች በምሳሌነት ቀርቦ በትምህርት መልክ ተሰጥቷቸዋል፡፡በሌላ በኩልም የጋራ፣ የግል እና ብዛት ባላቸው ግብ ጠባቂዎች መካከል የሚሰጡ ስልጠናዎች ምን አይነት እንደሆኑ እና ኢትዮጵያዊያን አሰልጣኞች ከታዳጊ፣ ወጣት እስከ አዋቂ ድረስ መከተል ስላለባቸው የስልጠና አማራጮች ገለፃ የተደረገ ሲሆን አንድን ግብ ጠባቂ ለማፍራት ተንከባክቦ ማሳደግ ላይ ትኩረት ማድረግ እንዳለባቸው ተገልጿል።በመጨረሻም ሰልጣኞቹ በስልጠናው ዙርያ ጥያቄዎች አንስተው በባለሙያዎቹ ምላሽ ከተሰጠ በኋላ መርሐ ግብሩ ተጠናቋል፡፡ | 0 |
13eceed03f1ceb49837e5cf779d59130 | 47a38d1fded2b6cf143bee909d0b2752 | 18 ባንኮች እና የፋይናንስ ተቋማት ለሀገር መከላከያ ሰራዊት ከ205 ሚሊየን ብር በላይ ድጋፍ አደረጉ | አዲስ አበባ ፣ ህዳር 8 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) “ለሀገር መከላከያ ክብር እቆማለሁ” መርሀ ግብር በሀገሪቱ የተለያዩ አካባቢዎች ተካሄዷል።የሶማሌ ክልል የካቢኔ አባላት ለሀገር መከላከያ ክብር እቆማለሁ መርሀ ግብርን ከረፉዱ 5:30 ላይ ለ1 ደቂቃ ቀኝ እጃቸውን በግራ ደረታቸው በማድረግ ለሀገር መከላከያ ሠራዊት ያላቸውን ክብር አሳይተዋል።የክልሉ የካቢኔ አባላት ለሀገር መከላከያ ሠራዊት ድጋፍ የሚውል 10 ሚሊየን ብር እና 2 ሺህ ፍየልና ሰንጋ ድጋፍ ማድረጋቸውን የሶማሌ ክልል ሬዲዮና ቴሌቪዥን ዘግቧል። | 0 |
68ea159e4f8df3565719215b4227c044 | 927ed8ceeb1b08f1bb62cb2862ca977b | ቦይንግ በአውሮፕላን አደጋ ሕይወታቸውን ላጡ ሰዎች ቤተሰቦች ካሳ ሊከፍል ነው | አዲስ
አበባ፡- የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከትናንት በስቲያ በደረሰው የአውሮፕላን አደጋ ህይወታቸውን ያጡ ሰዎች ቤተሰቦች ስለአደጋው ለማወቅ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው በሚያደርጉት ቆይታ ሙሉ ወጪያቸውን እንደሚሸፍንና አስፈላጊውንም ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታወቀ። የአየር መንገዱ ምክትል ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ኢሳያስ ወልደማርያም ትናንት በደረሰው አደጋ ዙሪያ በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ለተለያዩ ሀገራት ዲፕሎማቶች ማብራሪያ ከሰጡ በሁዋላ ለጋዘጠኞች እንደተናገሩት ፤ አየር መንገዱ እስከአሁን የተለያዩ መንገዶችን በመጠቀም በ35ቱም ሀገራት ለሚገኙ የሟች ቤተሰቦች ስለአደጋው መረጃዎችን ሲያደርስ ቆይቷ። በቀጣይም
ጉዳዩን ለማጣራት ወደ ኢትዮጵያ ለሚመጡ የሟች ቤተሰቦች አስፈላጊውን ድጋፍ ያደርጋል፤ ወጪንም ይሸፍናል። የትራንስፖርት ሚኒስቴር ፤ ሲቪል አቪይሽንና የአየር አደጋ ሲከሰት ለምርመራ ከሚቋቋም ቦርድ ጋር በመሆን የአደጋውን መንስኤ ለማወቅም ዓለም አቀፍ ህግጋትንና መመሪያዎችን በተከተለ አካሄድ እንደሚሠራም ገልጸዋል፡፡ ምክትል ዋና ሥራ አስፈጻሚው እንዳሉት፤ የማጣራቱ ሥራ ከተጠናቀቀም በኋላ አየር መንገዱ አስክሬኖችን ወደ ቤተሰባቸው ያደርሳል:፡ ምርመራው ተጀምሮ እስኪጠናቀቅም አደጋው የደረሰበት ቦታ አስፈላጊው ጥበቃ እየተደረገለት ይገኛል። ለጊዜው
የተለየ ችግር ባይኖረም ቀሪዎቹ ስድስቱ ቦይንግ 737 – 800 ማክስ አውሮፕላኖች ከአገልግሎት ታግደዋል፡፡ ‹‹ቦታውን እኛም የተጎጂ ቤተሰቦችም ማየት እንፈልጋልን›› የሚል ጥያቄ ከዲፕሎማቶቹ ቀርቦ እንደነበር አቶ ኢሳያስ ጠቅሰው፣ ጥያቄውን ውሳኔ ለሚሰጠው አጣሪ ቦርድ እንደሚያቀርቡም ተናግረዋል። በተመሳሳይ የሟቾች ሙሉ መረጃ ይሰጠን የሚል ጥያቄ እንደተነሳና ለጊዜው ለሟቾች ሀገራት በቻ እንደሚነገር አስታውቀዋል። የካሳ ጉዳይም ዓለም አቀፍ መመሪያዎችን በተከተለ ሁኔታ እንደሚፈጸም ተናግረው፣ ዲፕሎማቶቹ የአደጋውን መነሻ ለማጣራት ለሚደረገው እንቅስቃሴ አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ቃል መግባታቸውንም ገልጸዋል፡፡ አየር መንገዱ በ73 ዓመታት ታሪኩ በቴክኒክና በባለሙያ ስህተት ምንም ዓይነት አደጋ ደርሶበት አያውቅም ያሉት አቶ ኢሳያስ ፣ ዛሬም ደረስ በቀን 300 በረራዎች በማድረግ ሃያ ሺ የሚደርሱ መንገደኞችን እያጓጓዘ እንደሆነም ጠቁመዋል።አዲስ
ዘመን መጋቢት 3/2011በየራስወርቅ
ሙሉጌታ | 0 |
b2dbfabdacb8d26bfc9d163b9d156216 | 830d835447c5607d72922f3f60913111 | አዲስ ለተገነቡ የጋራ መኖሪያ ቤቶች የተዘረጋን የኤሌክትሪክ መስመር የሰረቁ ተጠርጣሪዎችን እጅ ከፍንጅ መያዙን ፖሊስ አስታወቀ | የአዲስ አበባ ቤቶች አስተዳደር ኤጀንሲ በ11ኛው ዙር የጋራ መኖሪያ ቤት እድለኞች ለሆኑ ዜጎች የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለመሥጠት ቅድመ ዝግጅቶችን ሙሉ ለሙሉ ማጠናቀቁን አስታወቀ ።የኤጀንሲው ሥራ አስኪያጅ አቶ ሽመልስ ታምራት በዛሬው ዕለት ለጋዜጠኞች በሠጡት መግለጫ እንደገለጹት ሐምሌ 30 /2008 ዓም የጋራ መኖሪያ ቤቶች የወጣላቸው ዜጎች በቦሌና በአቃቂ ክፍለ ከተሞች በተዘጋጁላቸው የአንድ ማዕከል አገልግሎት ለማስተናገድ የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች ተጠናቀዋል ።ከዚህ ቀደም በነበሩት የ10 ዙር የጋራ መኖሪያ ቤቶች የማስተላላፍ ሂደት የቤት ተጠቃሚዎች በርካታ እንግልትና ውጣውረዶች እንደሚያጋጥማቸው ያስታወሱት አቶ ሽመልስ በሚጀምረው የአንድ ማዕከል አገልግሎት አንድ የጋራ መኖሪያ ቤት ተጠቃሚ ቤቱን ለመረከብ አንድ ዓመት ሲፈጅበት የነበረው የማስተላላፍ ሂደት በአንድ ቀን ለማጠናቀቅ የሚያስችል ነው ብለዋል ።የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ የጋራ መኖሪያ ቤት ተጠቃሚ ነዋሪዎች ከዚህ ቀደም ቁልፍ ለመረከብ ፣ የይዞታ ካርታ ለመውሰድ ፣ ከባንክ ጋር የተያያዙ ውሎችን ለመፈጸም የሚፈጀውን ጊዜ በመቀነስ ሶስቱንም አገልግሎቶች በአንድ ማዕከል ፣ ዘመናዊና በተቀላጠፈ መልኩ አገልግሎትን ለመሥጠት የሚያስችል መሆኑን አቶ ሽመልስ አመልክተዋል ።የአንድ ማዕከል አገልግሎቱ ከመጪው ሰኞ መስከረም 9 እስከ ህዳር 19 ድረስ በቦሌና አቃቂ ቃሊቲ ክፍለ ከተማዎች በተዘጋጁት ማዕከላት አገልግሎቱ የሚሠጥ መሆኑን ያብራሩት አቶ ሽመልስ ማንኛውም የቤት እድለኛ የሚጠበቁበትን ቅድመ ሁኔታዎችን በሟሟላት በአጭር ጊዜ ውስጥ አገልግሎቱን ማግኘት እንደሚችል ገልጸዋል።አጀንሲው በ11ኛው የጋራ መኖሪያ ቤት ተጠቃሚዎችን የሚያስተናግደው የብሎክ ቁጥሮችን መሠረት አድርጎ በሚያወጣቸው የጊዜ ሰሌዳና መሆኑን የጠቆሙት አቶ ሽመልስ ማንኛውም ተገልጋይ የሚስተናገድበትን የጊዜ ሰሌዳ በየክፍለ ከተማዎች የሚለጠፍ መሆኑንና በአዲስአበባ አስተዳደር ድረገጽ ላይ መመልከት እንደሚችል አስረድተዋል ።በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የኮሚኒኬሽን ክፍል ሥራ አስኪያጅ አቶ ኤፍሬም መኩሪያ በበኩላቸው ባንኩ የጋራ መኖሪያ ባለዕድለኞች ሳይንገላቱ የብድር ውል አገልግሎት ለመሥጠት በቦሌና አቃቂ ክፍለ ከተማዎች ማዕከላት በመክፈቱ ጠቅሰው ለወደፊቱም ማዕከላቱን በተቀሩት ክፍለ ከተማዎች ለመክፈት ማቀዱን ተናግረዋል ። | 0 |
5653762e70367378c21503be22fe7f17 | 26c8864fbb38f226fc8096b6a7f12237 | የጋሞና የኦሮሞ ዕርቅ | የኦሮሞ ነፃነት ግንባር /ኦነግ/ በያዝነው ሣምንት መባቻ ላይ ባወጣው መግለጫ ከኢትዮጽያ መንግሥት ጋር የሚያካሄደውን ግጭት ለማስቆምና እርቅ ለማውረድ ወገንተኛ ያልሆነ ወይም ነፃ ሦስተኛ ወገን እንዲያደራድረው ጠይቋል።“መንግሥት ከአመራሩ ጋር የደረገውን ስምምነት አላከበረም፤ ጥቃት ከፍቶብኛል” በማለት ደጋግሞ ሲከስ ይሰማል።ክሡን የሚያስተባብለው የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ /ኦዴፓ/ በበኩሉ “ይልቅ ትጥቁን ቃል በገባው መሠረት ‘አልፈታም’ ያለው ኦነግ ነው፤ ታጣቂዎቹም ኦሮምያ ውስጥ ግድያ ላይ ተሠማርተዋል፤ ሥርዓተ-አልበኝነት አንግሠዋል” ይላል።ለመሆኑ የሁለቱ ወገኖች ስምምነት ጭብጥ ምንድነው? ውጊያውንስ ምን አመጣው? እንዴትስ እርቅ ይወርዳል ?የኦሮሞ ዴሞክራሲያዊ ፓርቲ /ኦዴፓ/ ማዕከላዊ ፅሕፈት ቤት የሕዝብ አስተያየትና የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ ታየ ደንደአና የኦሮሞ ነፃነት ግንባር ቃል አቀባይ አቶ ቶሌራ አደባ አሜሪካ ድምፅ ላይ ተወያይተዋል።ሙሉውን ውይይት ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ። | 0 |
107f19d32df6df2339d14cf56f8dae80 | c27a92d7eddacd11b7717d9c58708a2e | የቅዱስ ጊዮርጊስ እና ሀዋሳ ከተማ ጨዋታ ዛሬ እንዲደረግ ተወሰነ | በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ15ኛው ሳምንት መርሀ ግብር ቅዳሜ ሊደረግ የነበረው የቅዱስ ጊዮርጊስ እና የአዳማ ከተማ ጨዋታ ወደ ሰኞ ተሸጋግሯል፡፡የ2012 የኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ የ15ኛ ሳምንት የአንደኛው ዙር የመጨረሻ ጨዋታዎች በዚህ ሳምንት ይደረጋሉ፡፡ ከእነኚህ ጨዋታ መካከል በአዲስ አበባ ስታዲየም የፊታችን ቅዳሜ በ9:00 ሊደረግ የነበረው የቅዱስ ጊዮርጊስ እና የአዳማ ከተማ ጨዋታ ወደ ሰኞ 10:00 ተዛዋውሯል፡፡ የቀን ለውጡ ያስፈለገውም ቅዳሜ በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ የድምፀዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን የሙዚቃ ኮንሰርት በመኖሩ የፀጥታ አካላት በበቂ ሀኔታ ላይኖሩ ስለሚችሉ እንዲሁም ከተማዋ ላይ በአንድ ቀን ሌላ ፕሮግራም መኖር ስለሌለበት በሚል ነው ተብሏል።© ሶከር ኢትዮጵያ | 0 |
c3276be440b3f3a70493c6afd884811e | ee87d7cd6e9d24d1e7d496b3c97f487a | በ5 ወራት ብቻ 1 ቢሊየን 356 ሚሊየን 119 ሺህ ብር የሚገመቱ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ተይዘዋል | አዲስ አበባ፣ ህዳር 13፣ 2013 (ኤፍቢሲ) በተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በአንድ ሳምንት ብቻ 51 ነጥብ 9 ሚሊዮን ብር የሚገመት የኮንትሮባንድ ዕቃ በቁጥጥር ስር ዋለ፡፡ከዚህ ውስጥ ከ31 ሚየን ብር በላይ የሚገመተው ወደ ሀገር ሲገባ ሲሆን ከ20 ሚሊየን ብር በላይ የሚሆነው ደግሞ ከሀገር ለማስወጣት ሲሞከር ነው ተብሏል፡፡በቁጥጥር ስር የዋሉት የኮንትሮባንድ ዕቃዎች የቁም እንስሳት፣ የምግብ ምርቶች፣ ጌጣጌጥ፣ አልባሳት፣ ኤሌክትሮኒክስ እና አደንዛዥ ዕፅ ይገኙበታል፡፡በከፍተኛ መጠን ከተያዙ የኮንትሮባንድ ዕቃዎች ውስጥ በሞያሌ ቅርንጫፍ ስር በሚገኙ ሞያሌ፣ ያቤሎ፣ ነጌሌ ቦረና፣ ቡሌሆራ መስመር አድንዛዥ ዕፅ፣ በሀዋሳ ቅርንጫፍ ስር በሚገኙ ጢጢቻ፣ ጪጩ፣ ኮንሶ፣አዳባ፣ ዲላ መስመር ዘጠኝ ሚሊየን ብር የሚገመት የተለያዩ አልባሳት፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ ስጋራ፣ ኮስሞቲክስ፣ ልባሽ ጨርቅ፣ መለዋወጫ ናቸው፡፡እንዲሁም በሞያሌ ቅርንጫፍ ከ6 ሚሊየን ብር በላይ ሚገመት የተለያዩ አልባሳት፣ የምግብ ምርቶች፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ ሲጋራ፣ ኮስሞቲክስ፣ ልባሽ ጨርቅ፣ መለዋወጫ እንዲሁም በድሬደዋ ቅርንጫፍ ሀረር፤ ድሬደዋ፣ ለጋር፣ ቢዮቆቤና ደወሌ መስመር ከ3 ሚሊየን ብር በላይ የሚገመት የተለያዩ አልባሳት፣ ኤሌክትሮኒክስ፣ ሲጋራ፣ ኮስሞቲክስ፣ ልባሽ ጨርቅ፣ መለዋወጫ በቁጥጥር ስር ውለዋል፡፡እንዲሁም በባህርዳር ቅርንጫፍ ሰራቫ፣ ሻውራ፣ መተማ የመቆጣጠሪያ ጣቢያዎች 30 የብሬይን ጥይት፣ 166 የክላሽ ጥይት፣ 2 ሺህ 771 የአሜሪካን ዶለር በቁጥጥር ስር እንዲውል መደረጉን ከገቢዎች ሚኒስትር ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ሚኒስቴሩ ሁሉም ከተባበረ ለህገ-ወጦች የፋይናንስ ምንጭ የሚሆነውን የኮንትሮባንድ ንግድ በመግታት የሀገር ሰላምና ፀጥታ ማረጋገጥ ይቻላል ብሏል፡፡ | 0 |
573d67a371e559a7d1e51e706a731285 | d082751f16735fe28b1e7cd47aa1b7cc | መንግስት ህግ ለማስከበር በሚያደርገው ጥረት ሴቶች የነቃ ተሳትፎ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀረበ፡፡ | በአገሪቱ የተጀመረው የታሃድሶ ንቅናቄ ሂደት ውጤታማ የሚሆነው መላው የአገሪቱ ህዝቦች የማያቋርጥና የነቃ ተሳትፎ ሲያደርጉ መሆኑን የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማርያም ደሳለኝ ገለጹ ።ጠቅላይ ሚንስትር ኃይለማርያም በዛሬው ዕለት በሐረር ከተማ 11ኛው የብሔር ፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል ላይ ተገኝተው ባደረጉት ንግግር እንደገለጹት በአገሪቱ እየተካሄደ ያለው ጥልቅ ታሃድሶ ውጤት እንዲበቃ ሁሉም ህብረተሰብ ያሳተፈ ንቅናቄ ሲደረገ ነው ።በመሪው ፓርቲ ኢህአዴግና በአጋር ድርጅቶቹ የተጀመረው ጥልቅ የታሃድሶ ንቅናቄ መላው የህብረተሰብ ክፍሎችን ያካተተና የማደስ አቅምም እንዳለውና በቅርቡ የገጠሙትን የአስተሳሰብ ዝንባሌዎችና ጉድለቶችን ለመሙላት የሚያስችል መሆኑን ጠቅላይ ሚንስትሩ ገልጸዋል ።በኢትዮጵያ ህገ መንግሥት እንደተቀመጠው ዴሞክራሲያዊ አንድነትን ለማበልጸግ ላለፉት ዓመታት አጅግ አበረታች ሥራዎች እንደተካሄዱ ያስታወሱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦችን የጋራ ጥቅሞችን ለማስከበር ባለፉት 22 ዓመታት በአንድነትና በተደጋጋፊነት ለማሳደግ የተገባውን ቃል ኪዳን ተግባራዊ እየተደረገ መሆኑን ገልጸዋል ።የህገ መንግሥቱ ሰነድ ከጅማሬው አንስቶ የህዝቦችን መልካም እሴቶችን ፣ የጋራ ጥቅሞችንና አመልካከትን በማጎልበት አንድ ጠንካራ የኢትዮጵያን ማህበረሰብ ለመፍጠር ወሳኝ መሆኑ ታምኖበት ነው ብለዋል ።ዘንድሮ የ11ኛው የብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች ቀን በዓልን ስናከብር ህገ መንግሥቱን ስናጸድቅ የገባነውን ቃል ኪዳን በማጽናትና በተግባርም ለማስመስከር በማሰብ መሆኑን ው ያስገነዘቡት ጠቅላይ ሚንስትሩ በመተሳሰብና በመመካከር እንዲሁም የጋራ ተጠቃሚነት ላይ የተመሠረተ አገራዊ አንድነትን ይበልጥ ማጠናከር እንደሚገባ አስረድተዋል ።የህዝብና የመንግሥት ሃብትን አላግባብ ለግል ጥቅም የመዋል ዝንባሌንና ብልሹ አሠራሮችን ለመከላከልም በተለያዩ ደረጃዎች የሚካሄዱ ጥልቅ ታሃድሶዎችና እርምጃዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ ጠቅላይ ሚንስትሩ አያይዘው አስታውቀዋል ።በመጨረሻም ጠቅላይ ሚንስትሩ 11ኛው ብሔሮች፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል በድምቀት እንዲከበር ላደረገው የሐረሪ ብሔራዊ ክልል መንግሥትና ህዝብ ታላቅ ምስጋና አቅርበዋል ። የ11ኛው የብሔሮች ፣ ብሔረሰቦችና ሕዝቦች በዓል “ ህገ መንግስታችን፣ ለዴሞክራሲያዊ አንድነታችንና ለህዳሴያችን" በሚል መሪ ቃል የተከበረ ሲሆን 12ኛው የብሔሮች ፣ ብሔረሰቦችና ህዝቦች በዓል አዘጋጅነት ለአፋር ክልል ተሠጥቷል ። | 0 |
b63f2efe2476753d689529af5e20474f | b63f2efe2476753d689529af5e20474f | የፓኪስታን ፍ/ቤት በአንድ ተቃዋሚ መሪ ላይ ክስ መሰረተ | በተቃዋሚ መሪው ሻሀባዝ ሻሪፍ ላይ በዛሬው ዕለት የተመሰረተው ክስ፣ ላሆር ውስጥ ከሚገነባ የመኖሪያ ቤቶች ህንፃ ሥራ ጋር በተያያዘ ሲሆን፣ የቤቶቹን የሥራ ኮንትራት እርሳቸው አባል ለሆኑበት ለፓኪስታኑ የሙስሊም ሊግ ፓርቲ ሰዎች ሰጥተዋል ተብለው ነው።ከዚህ የሙስና ቅሌት ጋር በተያያዘ፣ ሌሎች 7 ሰዎችም ተከሰዋል። ይሁንና፣ ተጠርጣሪው የተቃዋሚ መሪ ሸሪፍ፣ «መሰረተ-ቢስ የሆነ የሀሰት ውንጀላ» በማለት፣ በአንድ የፓኪስታን ጋዜጣ ላይ በሰጡት ቃል አስተባብለዋል።የተጠርጣሪው ወንድምና የቀድሞው የፓኪስታን ጠቅላይ ሚኒስትር ናዋዝ ሻሪፍ እአአ በ2017 በሙስና ቅሌት ከሥልጣን መነሳታቸውን ልብ ይሏል! | 1 |
d811e60c22259da65ed15e3a126c0dfd | d811e60c22259da65ed15e3a126c0dfd | ዩናይትድ ስቴትስ በጋና ዜጎች ላይ የቪዛ ዕገዳ ጣለች | ዩናይትድ ስቴትስ በጋና ዜጎች ላይ የቪዛ ዕገዳ መጣሏን ስታስታውቅ፣ ዕርምጃው - ዩናይትድ ስቴትስን ለመጎብኘት የሚፈልጉ የዚያች የምዕራብ አፍሪካይቱ ሃገር ዜጎችን ጉዳይ ይበልጥ አስቸጋሪ ያደርገዋል ተብሏል።የትረምፕ አስተዳደር ዕገዳውን ያፀናው ጋና ከዩናይትድ ስቴትስ እንዲወጡ የታዘዙ ዜጎቿን ወደ ሃገራቸው መመለስ አልቻለችም ሲል በመክሰስ ነው።የዩናይትድ ስቴትስ የሃገር ውስጥ ደኅንነት መሥሪያ ቤት ኃላፊዋ ክሪስቲን ኒልሰን ስለዚሁ ባወጡት መግለጫ ጋና በዓለምቀፉ ሕግ መሠረት ከአሜሪካ እንዲወጡ የታዘዙ ዜግቿን የመቀበል ኃላፊነቷን አልተወጣችም ብለዋል። | 1 |
e972f3851886e873023eba6a193246be | e972f3851886e873023eba6a193246be | ‹‹ፓርኩ 1.5 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ ምርትወደ ውጭ ልኳል››-አቶ ጎይቶም ገብረኪዳን የመቀሌ ኢንዱስትሪ ፓርክ ሥራ አስኪያጅ | በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን በጀመረ በአጭር ጊዜ ውስጥ 1.5 ሚሊዮን ዶላር የሚያወጣ ምርት ወደ ውጭ ኤክስፖርት ማድረጉን የፓርኩ ሥራ አስኪያጅ አቶ ጎይቶም ገብረኪዳን ገለጹ። በመቀሌው ኢንዱስትሪ ፓርክ ሦስት ኩባንያዎች ወደ ሥራ ገብተው እስከ 2200 ሠራተኛ መቅጠራቸውን የነገሩን ሥራ አስኪያጁ ወደፊት ፓርኩ በሙሉ አቅሙ ማምረት ሲጀምር በሁለት ሺፍት ከአሥር እስከ 20ሺ ሠራተኞች እንደሚቀጠር ነግረውናል። አዲስ ዘመን ግንቦት 22/2011 | 1 |
b9af51a4721ae3671ddd0cd6fac5fc81 | e32f937279e6600302907fcdd7d986ba | በኮሎምቢያ ማረሚያ ቤት ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተያያዘ በተነሳ አመፅ ከ23 ሰዎች በላይ ሰዎች ለህልፈት ተዳረጉ | አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 28 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በብራዚል በኮሮና ቫይረስ ሳቢያ ለህልፈት የተዳረጉ ሰዎች ቁጥር 34 ሺህ መድረሱ ተገልጿል።ይህን ተከትሎም በሃገሪቱ በኮቪድ19 ለህልፈት የተዳረጉ ሰዎች ቁጥር ከአውሮፓዊቷ ጣሊያን መብለጡ ነው የተነገረው።እስካሁን ባለው ሂደትም ከአሜሪካ እና ብሪታንያ ቀጥሎ በርካታ ሰዎች በኮቪድ19 ምክንያት ለህልፈት የተዳረጉባት ሃገር ሆናለች።ከዚህ ባለፈም በሃገሪቱ ቫይረሱ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 580 ሺህ ደርሷል ነው የተባለው።ፕሬዚዳንት ቦልሶናሮ ከቫይረሱ ጋር በተያያዘ ይሰጡት የነበረውን አስተያየትና ሃሳብ ማቆማቸውም ነው የተገለጸው።ምንጭ፦ ቢቢሲ | 0 |
b2cb12abee24d6d2794797aac4fb1b8c | ac961e1f351a63b0cfab69e6e41b5e43 | “ህጉ ሀገራዊ ተወዳዳሪነትን ለማሳደግና ኢንቨስትመንት ለመሳብ ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረክታል”-መላኩ አለበል፣የንግድ ሚኒስትር | አዲስ አበባ፣ ሀምሌ 30 ፣2012 ( ኤፍ.ቢ.ሲ) በ2013 በጀት ዓመት 4 ነጥብ 5 ቢሊየን ዶላር የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ለመሳብ መታቀዱን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን አስታወቀ።የመሰረተ ልማት መጠናከር፣ በቀላሉ ሰልጥኖ ወደ ስራ መግባት የሚችል የሰው ሃይል፣ እየተመዘገበ ያለው ፈጣን የኢኮኖሚ እድገትና እምቅ የተፈጥሮ ሃብት በኢትዮጵያ ኢንቨስትመንትን ለመሳብ በምቹ አጋጣሚነት ከሚጠቀሱት መካከል መሆናቸው ተጠቅሷል።በሌላ በኩል የገበያ ተደራሽነት እያደገ መምጣትም የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት እንዲያድግ የበኩሉን አስተዋጽኦ እያደረገ ይገኛል ነው የተባለው።እነዚህንና ሌሎች መልካም አጋጣሚዎችን በመጠቀም በበጀት ዓመቱ 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ለመሳብ ታቅዷል።በውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንት ለስኬት የሚያበቁ ምቹ ሁኔታዎችን ግምት ውስጥ በማስገባት እቅዱ መያዙን የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን የኦፕሬሽን ዘርፍ ምክትል ኮሚሽነር አቶ አንተነህ አለሙ ተናግረዋል።የቂሊንጦ የመድሐኒት (ፋርማሲዩቲካል) ኢንዱስትሪ ፓርክ ባለፈው ዓመት ግንባታው ተጠናቆ ወደ ስራ መግባቱ የሚታወስ ነው።በመሆኑም በፓርኩ የመድሐኒት አምራችነት መሳተፍ የሚፈልጉ ባለሀብቶች ወደ ስራ ይገባሉ ተብሎ ይጠበቃል።ይህም አይነተኛ የኢንቨስትመንት መሳቢያ አማራጭ ሆኖ ለተያዘው እቅድ ስኬት ትልቅ ተስፋ የተጣለበት መሆኑን አቶ አንተነህ ገልጸዋል።ኮቪድ-19 ወረርሽኝ ከተከሰተ በኋላ በዓለም የምግብ ነክ ምርቶች ፍላጎት መጨመሩንና ይህንንም ታሳቢ በማድረግ የተቀናጀ የግብርና ማቀነባበሪያ ኢንዱስትሪ ፓርኮች በስፋት ወደ ምግብ ምርት እንዲገቡ ይደረጋል ብለዋል።አዲስ የኢንቨስትመንት አማራጭ ከመፈለግ ባለፈ የአገር ውስጥ ባለህብቶች ኢንቨስትመንትን የሚያሳድጉ ስራዎች እንደሚሰሩና ለዚህም አስፈላጊው ድጋፍ እንደሚደረግ አመልክተዋል።የኢትዮጵያን የኢንቨስትመንት አማራጮችና እድሎችን የማስተዋወቅ ስራም በስፋት ይከናወናል ብለዋል።በኢንቨስትመንት ተቋማት የኮቪድ-19 ወረርሽኝ የሚያስፈልገው የጤና ጥንቃቄ እርምጃዎችና ቫይረሱን ለመከላከል የሚያስፈልጉ ቁሳቁሶችን የማሟላት ስራ ትኩረት ተሰጥቶ እንደሚሰራም ተናግረዋል።በ2012 በጀት ዓመት 4 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ለማግኘት ታቅዶ 2 ነጥብ 5 ቢሊዮን ዶላር ገቢ መገኘቱን ኢዜአ ዘግቧል ።
የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ። | 0 |
7ec8f4c9bc83343e1d18551255b95ed7 | 9d856cab626732b522af54907cd35b9c | የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፒዮ ከኦማኑ ሱልጣን ጋር ተወያዩ | አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 1 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የአሜሪካው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማይክ ፖምፔዮ በቀጣዩ ሳምንት እስራኤልን ሊጎበኙ ነው።የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት እንዳስታወቀው ጉብኝቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ የዌስት ባንክ የተወሰኑ ክፍሎችን ለመያዝ በሚያደርጉት ጥረት ዙሪያ ላይ ያተኮረ ውይይት ለማድረግ ያለመ ነው።በጉብኝታቸውም ከኔታንያሁ ጋር የጥምር መንግስት ለመመስረት ከተስማሙት ቤኒ ጋንትዝ ጋርም ይመክራሉ ተብሎ ነው የሚጠበቀው።ከዚህ ባለፈም አሜሪካ እና እስራኤል ኮቪድ19ኝን ለመከላከል በሚያደርጉት ጥረትና በቀጠናዊ የደህንነት ጉዳዮች ዙሪያ እንደሚወያዩም ይጠበቃል።ጉብኝቱ የፊታችን ረቡዕ ለአንድ ቀን እንደሚካሄድም የአሜሪካ ውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት አስታውቋል።ምንጭ፦ አልጀዚራ | 0 |
d26b21759e43e8f5649e76978988c6ba | f273df9fb57afca4ca272b294118d7e3 | Walias Intensify Their Preparation | The draw for the 2022 Qatar world cup African zone preliminary round has been conducted Today in Cairo, Egypt. Ethiopia is set to play Lesotho in between 2 and 10 September over two legs. Ethiopia and Lesotho were on the same qualifying group “J” in 2017 AFCON qualifiers staged in Gabon, the Walias were victories on both outings with 2-1 being the scoreline. Todays draw saw 28 lowest-ranked teams in the latest FIFA ranking tied to book a place in the 14 teams spot that is up for grabs for the 28 teams and those 14 teams will sum up with the rest 26 teams of better FIFA ranking who were automatically seeded in the list of 40 teams that in the near future will be split in to 10 groups of four, the winners of each group will earn the right to compete for a place in 2022 Qatar World Cup after a playoff match between them.2022 World Cup preliminary round drawEthiopia v LesothoSomalia v ZimbabweEritrea v NamibiaBurundi v Tanzania Djibouti v EswatiniBotswana v MalawiThe Gambia v AngolaLiberia v Sierra LeoneMauritius v Mozambique Sao Tome e Principe v Guinea-BissauSouth Sudan v Equatorial GuineaComoros v TogoChad v Sudan Seychelles v Rwanda | 0 |
61491ee7a650ca8432dc038bfffff38f | ffe0082a3c86679c436e6245df3f0c73 | የቱኒዚያው ፕሬዚዳንት የዶናልድ ትራምፕን የመካከለኛው ምስራቅ የሰላም እቅድ ተቹ | በዜናው መሰረት የሥድሳ ሰባት ዓመቱ ሙርሲ ህይወታቸው ያለፈው በመንግሥታዊ ሥለላ ወንጀል ክስ ፍርድ ቤት ችሎት ላይ ቀርበው ራሳቸውን ከሳቱ በኋላ ነው። ሆስፒታል ሳይደርሱ በፊት ህይወታቸው ማለፉን ነው ዜናው የገለፀው።በሙስሊም ወንድማማቾች ቡድን ውስጥ ከፍተኛ የመሪነት ቦታ የነበራቸው ሞሃመድ ሙርሲ እኤአ በ2013 በአስተዳደራቸው ላይ በተቀሰቀሰው ተቃውሞ የጦር ሰራዊቱ ከሥልጣን እንዳስወገዳቸው ይታወሳል።ከዚያም በቀደመው ዓመት በፕሬዚዳንታዊ ምርጫው ለመወዳደር ባስገቡት የዕጩነት ማመልከቻ ዋሽተዋል ተብሎ በቀረባበቸው ክስ የሰባት ዓመት እስራት ተፍርዶባቸው ከዚያ በኋላ የመንግሥታዊ ሥለላ ወንጀል ክስ ተከፍቶባቸዋል።ሂዩማን ራይጽ ዋች ክሱን በፖለቲካ የተነሳሳ ብሎታል። ሞርሲ እጅግ ጭካኔ በተመላበት እና ኢሰብዓዊ በሆነ አያያዝ ቤተሰብ እንዲጎበኛቸውም ሆነ የህክምና ዕርዳታ እንዳያገኙ ተደርጎዋል ሲሉ የሰብዓዊ መብት ድርጅቱ የመካከለኛው ምስራቅ ዋና ዳይሬክተር ሳራ ሊያ ዊትሰን ዛሬ በትዊተር ፅፈዋል። | 0 |
5742f915e28a3aab7474218b336ff25f | bbe69f93cac0e24d8b87a4d8afc8b2c6 | አፍሪቃ በጋዜጦች | “አፍሪካ በጋዜጦች” የተሰኘው ፕሮግራማችን ስለ አፍሪካ ከተፃፉት፣ የተወሰኑትን ጨምቆ ያቀርባል።የኢትዮጵያው ትግራይ ክልል በመልሶ ማልማት ጥረቱ የወርቅ ሽልማት አገኘ፣ ኢትዮጵያ ላይ በተዳጋጋሚ በደረሰው ድርቅ ምክንያት በሚልዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች አስቸኳይ የምግብ ረድዔት እንደሚያስፈላጋቸው ታወቀ፣ የአንጎላ ገዢ መደብ ፖርቱጋል ላይ ገንዘብ እያፈሰሰ መሆኑ ተገለፀ፡፡ | 0 |
07d6d84395eafc746d880f6625a72cda | 0ff5e076a7cfd0e0d7665c34512a9173 | ቢኒያም በላይ ወደ ሌላው የስዊድን ክለብ አምርቷል | ዳኛቸው በቀለ ለአዳማ ከተማ ከመፈረሙ በፊት በድሬዳዋ ከተማ የተጫወተ ሲሆን አምና ኢትዮጵያ ንግድ ባንክን ቢቀላቀልም የቋሚ ተሰላፊነት እድል ማግኘት አልቻለም ነበር፡፡ዳኛቸው ለድሬዳዋ ከተማ በዝውውር መስኮቱ የፈረመ 4ኛው ተጫዋች ሆኗል፡፡ አማካዩ አድናን ቃሲም ፣ ጋናዊው ተከላካይ ኢማኑኤል ላሬያ እና ሌላው ጋናዊ አጥቂ ሀምዛ መሀመድ ለብርቱካናማዎቹ የፈረሙ ተጫዋቾች ናቸው፡፡ | 0 |
943a9b5c6ce9506cc46ee1b128d74ccb | 943a9b5c6ce9506cc46ee1b128d74ccb | ዶ/ር ሊያ ታደሰ በፈለገ ሕይወት ሆስፒታል ጉብኝት አደረጉ | የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በባህር ዳር በሚገኘው ፈለገ ሕይወት ሆስፒታል የንፁህና ደህንነቱ የተጠበቀ ሆስፒታል የማድረግ እንቅስቃሴን ጎበኙ፡፡ሚኒስትሯ በማህበራዊ ገፃቸዉ እንደገለፁት በኤሌክትሮኒክስ የታገዘ የጤና መዛግብት አፈፃፀም እና የአገልግሎት መስጫ ቦታዎች ህሙማንን ማዕከል ያደረጉ እንዲሆኑ ለማስቻል የተሰራውን ስራም ጎብኝተዋል፡፡በጉብኝታቸው ወቅትም በቁርጠኝነት የሚሰሩ የሆስፒታሉንና የክልሉ ጤና ቢሮ አመራሮችንና ሰራተኞችን አመስግነዋል፡፡ | 1 |
98f73d461fc8411bf3f737d9eb42a7db | bff961b3aa20b8170017202c5ee15659 | በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል በኢንቨስትመንት የተሠማሩ ባለሃብቶች ውጤት ማስመዝገብ ጀምረዋል- አቶ አሻድሊ ሀሰን | አዲስ አበባ ፣ ግንቦት 28 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ እና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ከፍተኛ የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች የመተከልና አካባቢው ኮማንድ ፖስት አፈጻጸምን በተመለከተ በባሕር ዳር ተወያይተዋል።አፈጻጸሙ የተገመገመው የአማራ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አቶ ተመሥገን ጥሩነህና የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መሥተዳድር አቶ አሻድሊ ሐሰን በተገኙበት ነው።ውይይቱ የሁለቱ ክልሎች ተቀራርቦ የመሥራት ውጤትም ቀጠናው ከዚህ በላይ ሰላማዊ እና የሕግ የበላይነት የተረጋገጠበት እንዲሆን እንደሚያስችለው ታምኖበታል።በሁለቱ ክልሎች አጎራባች አካባቢዎች በነበረው አለመረጋጋት ከ49 ሺህ በላይ ሰዎች ተፈናቅለው እንደነበር የአማራ ክልል አደጋ መከላከል፣ ምግብ ዋስትናና ልዩ ድጋፍ የሚሹ አካባቢዎች ማስተባበሪያ ኮሚሽን መግለጹ ይታወሳል።ባለፉት ወራት በቀጠናው አንጻራዊ ሰላም መፈጠሩን ተከትሎ ደግሞ ከ30 ሺህ በላይ ሰዎች ወደ ቀያቸው እንደተመለሱ መገለፁን አብመድ ዘግቧል። | 0 |
782848f5a95ee088e07ea203ac57a5f5 | 782848f5a95ee088e07ea203ac57a5f5 | 693 የህግ ታራሚዎች በይቅርታና በምህረት ተፈቱ | 693 የህግ ታራሚዎች በይቅርታና በምህረት መፈታታቸውን የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር አስታወቀ።አስተዳደሩ ለኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት በላከው መግለጫ እንዳስታወቀው ታራሚዎች የጸደቀውን የምህረት አዋጅ መነሻ በማድረግ ሲፈቱ የመጀመርያው ነው።የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 1096/2010 የምህረት አዋጅን ማጽደቁ ይታወሳል።ዛሬ የተለቀቁት ታራሚዎችም በአዋጁ አንቀጽ 5 ሥር በተዘረዘሩ በህገ-መንግስቱ ስርዓት ላይ የሚደረግ ወንጀል፣ የህገ-መንግስታዊ ስልጣንን ተግባራዊነት ማሰናከል፣ የጦር መሳሪያ ይዞ በማመጽ የእርስ በእርስ ጦርነት ማስነሳት፣ የአገር ክህደት ወንጀል፣ የስለላ ወንጀል፣ የአገር መከላከያ ኃይልን መጉዳት በሚል በተዘረዘሩ ወንጀሎች የተከሰሱ ነበሩ።በቀጠሮ ላይ የሚገኙ 63 የቀጠሮ እስረኞችና 146 የተፈረደባቸው በድምሩ 209 የህግ ታራሚዎች በምህረት አዋጅ ህጉ መሰረት ዛሬ እንዲለቀቁ መደረጉን ነው አስተዳደሩ ያስታወቀው።በማረሚያ ቤት ቆይታቸው ባሳዩት መልካም ባህሪ በተለያዩ የወንጀል አይነቶች የተከሰሱና በፍርድ ቤት ውሳኔ ጥፋተኛ ተብለው የተፈረደባቸው የህግ ታራሚዎችና የቀጠሮ እስረኞች በይቅርታ አዋጅ ቁጥር 840/2006 መሰረት ለ484 የህግ ታራሚዎች መንግሥት ይቅርታ በማድረጉ ከማረሚያ ቤት እንዲወጡ ተደርጓል።አስተዳደሩ በመግለጫው እንዳመለከተው በአጠቃላይ 693 የህግ ታራሚዎች በምህረትና በይቅርታ ከማረሚያ ቤት ወጥተዋል።ከዚህ በፊት የህግ ታራሚዎች በማረሚያ ቤት ቆይታቸው በሚያሳዩት መልካም ባህሪ በተለያዩ ጊዜያት ከማረሚያ ቤት ወጥተው ወደ ማህበረሰቡ ሲቀላቀሉ መቆየታቸውን ያስታወሰው መግለጫው የምህረት አዋጁ ከጸደቀ በኋላ መንግስት ለታራሚዎች ይቅርታ ሲያደርግ ይህ የመጀመርያው መሆኑን ጠቁሟል።ኅብረተሰቡ የተለቀቁ ታራሚዎችን ተቀብሎ እንደማንኛውም ዜጋ ተገቢውን ክብር በመስጠት በተለያዩ ሥራዎች እንዲሰማሩ የበኩሉን ድጋፍ እንዲያደርግም ነው የፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ጥሪ ያቀረበው።የህግ ታራሚዎቹም ወደ ኅብረተሰቡ ሲቀላቀሉ ያዳበሩትን መልካም ባህሪ የበለጠ በማጠናከርና ራሳቸውን ከወንጀል በማራቅ የኢትዮጵያን የልማት ጉዞ በመደገፍ የድርሻቸውን እንዲወጡም ጠይቋል። (ኢዜአ) | 1 |
566c81a50f500f606d9328d24702bf4c | 978e77ce9e247616de8b5781345aeb38 | በህወሓት ውስጥ ያለው ቡድን በርካታ ነዋሪዎችን አፍኖ በመውሰድ ሰውሯቸዋል- የዳንሻ ከተማ ነዋሪዎች | የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ድሪባ ኩማ ረቡዕ ሚያዝያ 3 ቀን 2010 ዓ.ም. አስተዳደራቸው ጉልህ ሥፍራ ከሚሰጣቸው ፕሮግራሞች አንዱን ጎብኝተዋል፡፡ ከንቲባ ድሪባ ከከፍተኛ የከተማው ባለሥልጣናት ጋር ሆነው የጎበኙት በአዲስ አበባ ከተማ ከደኅንነት ወለል በታች የሚገኙ ነዋሪዎችን ለማቋቋም በዓለም ባንክ የሚደገፈውን ግዙፍ ፕሮግራም ነው፡፡ ይህ ፕሮግራም በ2009 ዓ.ም. የተጀመረ ሲሆን 123 ሺሕ ተጠቃሚዎችን አቅፏል፡፡ በዚህ ዓመት ደግሞ ይህ ቁጥር ወደ 200 ሺሕ የሚያድግ ሲሆን፣ የደሃ ደሃ የተባሉ ነዋሪዎች በሁለት መንገድ ለማቋቋም ያለመ ነው፡፡ የመጀመርያው አቅም እያላቸው የሥራ ዕድል ያልተፈጠረላቸውን ነዋሪዎች በአካባቢ ፅዳት፣ በአረንጓዴ ልማት፣ በተፋሰስ ልማት፣ በከተማ ግብርና ልማትና በመሳሰሉት ዘርፎች በማሰማራት ክፍያ እንዲያገኙ ማድረግ ነው፡፡ ሁለተኛው ደግሞ አቅመ ደካማ የሆኑ ነዋሪዎችን ቀጥታ የደመወዝ ተከፋይ በማድረግ ኑሮአቸው እንዲስተካከል ማድረግ ላይ ትኩረት ያደረገ ነው፡፡ ጉብኝቱ ከተካሄደባቸው ቦታዎች መካከል በጉለሌ ክፍለ ከተማ ጫካ ሚካኤል አካባቢ 21 ሔክታር መሬት ላይ የተሠሩ የተፋሰስ ልማት ሥራዎች ይገኙበታል፡፡ ከንቲባ ድሪባ ፕሮግራሙ መልካም ጅማሮ ማሳየቱን ሲገልጹ፣ በፕሮግራሙ የታቀፉ ነዋሪዎች ደግሞ ክፍያው አነስተኛ መሆኑን በመግለጽ እንዲሻሻል ጠይቀዋል፡፡ ከንቲባው የነዋሪዎችን ጥያቄ በመቀበል በቅርቡ ክፍያው በ15 በመቶ እንደሚያድግ ተናግረዋል፡፡ በአዲስ አበባ በአገር አቀፍ ደረጃ የከተሞች የምግብ ዋስትና ፕሮግራም የተዘረጋ ሲሆን፣ ከመንግሥትና ከዓለም ባንክ 450 ሚሊዮን ዶላር በጀት የተመደበለት ግዙፍ ፕሮግራም ነው፡፡ በምሥሉ ላይ ከንቲባ ድሪባ ኩማና የሥራ ባልደረቦቻቸው የተፋሰስ ልማት ሥራዎችን ሲጎበኙ ይታያል፡፡ | 0 |
98e440e2e0668f5037b5017c13da6c22 | 8339e2f28da6cc8b37fc9ad85b361f82 | ወላይታ ድቻ የቀድሞ አሰልጣኙ ወደ ስራ እንዲመለሱ ጥሪ አቀረበ | ወላይታ ድቻ አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ እና ረዳታቸው ግዛቸው ጌታቸውን ከዋናው ቡድን አሰልጣኝነት ማሰናበቱን የክለቡ ስራ አስኪያጅ አቶ አሰፋ ለሶከር ኢትዮጵያ አስታወቁ፡፡ወላይታ ድቻን ከ2001 ጀምሮ ሲያሰለጥኑ የቆዩትና አምና የጥሎ ማለፉን ዋንጫ እንዲያነሳ የረዱት አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ቡድኑ በውጤት ቀውስ ውስጥ መሆኑን ተከትሎ እንዲሰናበቱ መወሰኑን አቶ አሰፋ ገልፀዋል፡፡ወላይታ ድቻ ከአሰልጣኝ ስንብቱ በተጨማሪ ረዳት አሰልጣኙ ግዛቸው ጌታቸውን ወደ ወጣት ቡድኑ አሰልጣኝነት ወርዶ እንዲሰራ ሲወስን የቡድን መሪ ሆነው ሲሰሩ የነበሩት አቶ አሰፋ ሀሊሶ በስራ አስኪያጅነት ብቻ እንዲሰሩ እንዲሁም ሐብታሙ ኃይለሚካኤል ከቴክኒክ ዳይሬክተርነታቸው ጎን ለጎን የቡድን መሪነቱን ደርበው እንዲሰሩም ተወስኗል፡፡አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ከስንብቱ በኋላ ለሶከር ኢትዮጵያ በሰጡት አስተያየት በድቻ ለነበራቸው መልካም የስራ ጊዜያት ክለቡን አመስግነዋል፡፡ ‹‹ በክለቡ በነበረኝ ጊዜያት ደስተኛ ነበርኩ፡፡ ለ9 አመታት በነበረኝ ረጅም ቆይታም ከቡድኑ ጋር ብዙ ነገር ተምሬያለሁ፡፡ ስቀጠር እንደተደሰትኩት ሁሉ ስሰናበትም በደስታ ነው ከቡድኑ ጋር የምለያየው፡፡ ከጎኔ ለነበሩት እና ላገዙኝ የክለቡ አመራሮች እና ደጋፊዎች ሁሉ በፈጣሪ ስም አመሰግናለሁ፡፡ በቀጣይም ቡድኑ ውጤት እንዲያስመዘገብ እና ለቀጣዩ አሰልጣኝም መልካም እድል እንዲገጥመው እመኛለሁ፡፡›› ብለዋል፡፡ባለፈው ሳምንት ወደ ዋናው ቡድን ረዳት አሰልጣኝነት ተሸጋግሮ የነበረው አሰልጣኝ ዘነበ ፍስሃ ቡድኑን በጊዜያዊ ዋና አሰልጣንነት እንዲመሩ ውሳኔ ማስተላለፉ ታውቋል፡፡ አሰልጣኝ ዘነበ የ17 አመት በታች ቡድኑ ዋና አሰልጣኝ በመሆን ሲሰሩ የቆዩ አሰልጣኝ ናቸው፡፡ ደለለኝ ደቻሳ ደግሞ የአሰልጣኝ ዘነበ ረዳት ሆነው እንደሚሰሩ ከክለቡ ያገገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡በሊጉ በማሰልጠን ላይ ከነበሩ አሰልጣኞች መካከል ለረጅም አመት በአንድ ክለብ ቀዳሚ የነበሩት አሰልጣኝ መሳይ ተፈሪ ስማቸው ከአርባምንጭ ከተማ ዋና አሰልጣኝነት ጋር በስፋት ተያይዞ ይገኛል፡፡ | 0 |
c6808d296c8d7d2eaf1b1f057ec97462 | d235d72684f22874c356d9626fdbd175 | ከፍተኛ ሊግ | ገላን ከተማ ሁለት ተጨማሪ ተጫዋቾች ወደ ቡድኑ ቀላቅሏል | በከፍተኛ ሊግ ምድብ ሐ እየተወዳደረ የሚገኘው ጅማ አባ ቡና የቀድሞ አሰልጣኙን መልሶ ሲቀጥር ሦስት አዳዲስ ተጫዋቾችን ወደ ቡድኑ ቀላቅሏል።አሰልጣኝ አንተነህ አበራ ለሶስተኛ ጊዜ ወደ ቡድኑ ተቀላቅለዋል። በባለፈው ዓመት የአሰልጣኝ ግርማ ሐብተዮሐንስን ስንብት ተከትሎ አባቡናን በመረከብ በከፍተኛ ሊጉ እስከ መለያ ጨዋታው ማድረስ ቢችሉም በአወዛጋቢ ሁኔታ ከቡድኑ ከተለያዩ በኋላ በድጋሚ የአሰልጣኝ መኮንን ማሞ ስንብት ማግስት ወደ ጅማ አባቡና ተመልሰዋል።አሰልጣኝ አንተነህ በዘንድሮው የከፍተኛ ሊግ በምድብ ሐ በ13 ነጥቦች ዘጠነኛ ደረጃን በመያዝ የመጀመሪያውን ዙር ያጠናቀቀው ጅማ አባ ቡናን ወደ ተፎካካሪነት የመመለስ ኃላፊነት ተጥሎባቸው።ጅማ አባ ቡና ከአሰልጣኝ በተጨማሪ ሦስት አዳዲስ ተጫዋቾችን ወደ ቡድኑ ቀላቅሏል። ከደደቢት የለቀቀው የአጥቂ መስመር ተጫዋቹ ምስጋናው መኮንን በካርሎስ ዳምጠው ላይ ጥገኛ የሆነው የአጥቂ ክፍሉን እንደሚያጠናክር ሲጠበቅ በአማካይ ስፍራ ላይ ታከለ ታንቶን ከወልቂጤ ከተማ፣ ጅላሉ ከማልን ከአውስኮድ ማስፈረም ችለዋል። ከታዳጊ ቡድኑ ደግሞ አይመል ሸምሰዲን ኤና ተመስገን ድንቁን ወደ ዋናው ቡድን አሳድገዋል፡፡ | 0 |
af5e6f7433ddbdddfc7d3d10a94b6f2a | e5a95a424caf7d89ea2e6133caa4671e | በቂሊንጦ ማረሚያ ቤት ለደረሰው ጉዳት የማረሚያ ቤቱ አስተዳደር አባላት በሕግ እንዲጠየቁ ሐሳብ ቀረበ | ኢትዮጵያ ውስጥ በተለያዩ የሃገሪቱ ክፍሎች በሚገኙ ማረሚያ ቤቶች አለመረጋጋትና የእሣት ቃጠሎ እየደረሰ መሆኑ ይዘገባል።ባለሥልጣናት ለችግሩ ምክንያት - የመንግሥቱን የምህረት አዋጅ ተከትሎ ለታራሚዎች የሚሰጡ ትርጉሞች መዛባት መሆናቸውን ይናገራሉ።በደብረማርቆስ ማረሚያ ቤት ትላንት የተነሳውን የእሳት ቃጠሎ አስመልክቶ - ሰሎሞን ክፍሌ ወደ አማራ ክልል ጽሕፈት ቤት ደውሎ ነበር።የመንግሥት ኮሚኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ ሃላፊውን አቶ ንጉሡ ጥላሁንን አነጋግሯል።። | 0 |
5e5432265dec741ba948cad1ea76e22e | 1d2b2fa9a99d4ba03898a50d973202d5 | ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ 6 ተጫዋቾችን አስፈረመ | FT ባህርዳር ከተማ ፋሲል ከተማ (ባህርዳር)FT መቀለ ከተማ ኢትዮጵያ ውሃ ስፖርት (ውቅሮ)FT ሰሜን ሸዋ ደብረብርሃን ሱሉልታ ከተማ (ደብረብርሃን)FT አክሱም ከተማ አዲስ አበባ ፖሊስ (አክሱም)FT ወልድያ ሰበታ ከተማ (ወልድያ)FT ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ ኢትዮጵያ መድን (አዲግራት)FT አማራ ውሃ ስራ ቡራዩ ከተማ (ባህርዳር)ወሎ ኮምቦልቻ ከ ሙገር ሲሚንቶ (ኮምቦልቻ)FT ሻሸመኔ ከተማ ነቀምት ከተማ (ሻሸመኔ)FT ጅማ ከተማ ናሽናል ሴሜንት (ጅማ)FT አርሲ ነገሌ ሀላባ ከተማ (አርሲ ነገሌ)FT ድሬዳዋ ፖሊስ ፌዴራል ፖሊስ (ድሬዳዋ)FT አአ ዩኒቨርሲቲ ነገሌ ቦረና (አበበ ቢቂላ)አአ ከተማ ከ ጅንካ ከተማ (አበበ ቢቂላ)ደቡብ ፖሊስ ከ ባቱ ከተማ (ሀዋሳ)ወራቤ ከተማ ከ ጅማ አባ ቡና (ወራቤ) | 0 |
6da5991640bf2a188c7a707d5cf0df59 | afa1379a48f3dc54560eea633b9070e4 | በቴክሳስ ህገወጥ ስደተኛ ተማሪዎች ከትምህርት ቤት እንዲባረሩ የጠየቀችው መምህርት ከሥራዋ ተሰናበተች | ባሕር ዳር፡ ሚያዝያ 14/2012 ዓ.ም (አብመድ) የኮሮና ወረርሽኝ የዓለም ትልቅ የጤና ስጋት ሆኖ ለበርካታ ማኅበራዊ ግንኙነቶች መቋረጥ ምክንያት ሆኗል፤ ትምህርት ቤቶችም ተዘግተዋል፡፡ ነገር ግን ብዙ ተማሪዎች በየቤታቸው ሆነው በሬዲዮና በቴሌቪዥን የሚተላለፉ ትምህርቶችን ከመከታተልና ከማጥናት ይልቅ ከቤት ውጭ በጋራ ተሰባስበው እየተስተዋሉ ነው፡፡የመንግሥት ተቋማትና የግል ድርቶች የ‘ዋይ-ፋይ ኔትወርክ’ ባለመዝጋታቸው ተማሪዎቹ በእነዚህ ተቋማት አጥሮች ተሰባስበው እየዋሉ ነው፡፡ ይኼንን ነገር ለማስቀረት ማን ምን ማድረግ አለበት ትላላችሁ? | 0 |
ff79f285ab7daa491dd2257cc9bc1bbd | dc0b8908442e0cabf5fcd8579e1f3064 | ተመድ የሊቢያ ተቀናቃኝ ኃይሎች ዘላቂነት ያለው የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ መድረሳቸውን አስታወቀ | አዲስ አበባ ፣ መስከረም 30 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) አርመኒያ እና አዘርባጃን በናጎርኖ ካራባህ ግዛት ጊዜያዊ የተኩስ አቁም ለማድረግ ተስማሙ፡፡የሩሲያው የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰርጌ ላቭሮቭ ሁለቱ ሃገራት በሞስኮ ለ10 ሰአታት ከተወያዩ በኋላ የተኩስ አቁም ለማድረግ መስማማታቸውን አስታውቀዋል፡፡ከስምምነቱ መደረስ በኋላም ሃገራቱ ገንቢ ውይይት ያደርጋሉም ነው ያሉት ላቭሮቭ፡፡የተኩስ አቁም ስምምነቱን ተከትሎም ሃገራቱ ከዛሬ ጀምሮ የእስረኞች ልውውጥ የሚያደርጉ ይሆናል፡፡የአዘርባጃን አካል እንደሆነች የሚነገርለትና የግጭታቸው መንስኤ የሆነው ናጎርኖ ካራባህ ግዛት በአርመኒያውያን ይተዳደራል፡፡ሁለቱ ሃገራት ከፈረንጆቹ 1988 እስከ 1994 ድረስ በክልሉ ይገባኛል ጉዳይ ጦር ተማዘው ነበር፡፡ከዚያን ጊዜ ወዲህ ግጭት ውስጥ ባይገቡም በክልሉ የባለቤትነት ጉዳይም ሆነ በሰፈራ ፕሮግራም ላይ ግን ምንም አይነት ስምምነት ደርሰው አያውቁም፡፡የዛሬ ሁለት ሳምንት ዳግም በጀመረው የሁለቱ ሃገራት ግጭት ሳቢያም እስካሁን ከ300 በላይ ሰዎች ለህልፈት ሲዳረጉ በሺዎች የሚቆጠሩት ደግሞ መፈናቀላቸው ይነገራል፡፡ምንጭ፦ ቢቢሲ | 0 |
91aae5b604abba1295e237cc871f478f | 91aae5b604abba1295e237cc871f478f | በህግ ቁጥጥር ስር በዋሉ 4 ሺህ 183 ተጠርጣሪዎች ላይ ክስ ተመሰረተ | አዲስ አበባ ፣ መስከረም 20 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) ከአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ግድያ ጋር ተያይዞ በህግ ቁጥጥር ስር በዋሉ 4 ሺህ 183 ተጠርጣሪዎች ላይ ክስ መመስረቱን የኦሮሚያ ጠቅላይ ዐቃቤ ህግና የኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን አስታወቁ፡፡የኦሮሚያ ክልል ጠቅላይ ዐቃቤ ህግ ሁሴን ዑስማን እና በኦሮሚያ ፖሊስ ኮሚሽን ምክትል የወንጀል መርማሪ ኮሚሽነር ግርማ ገላን በጋራ በሰጡት መግለጫ የአርቲስቱን ግድያ ተከትሎ በተፈጠረ ግርግር የ167 ሰዎች ህይወት ሲጠፋ በ360 ሰዎች ላይ ደግሞ የአካል ጉዳት መድረሱን ገልጸዋል፡፡ከዚህ ባለፈም ከ4 ነጥብ 6 ቢሊየን ብር በላይ የሚገመት ንብረት መውደሙንም ተናግረዋል፡፡ከዚህ ጋር ተያይዞ የ9 ሺህ 63 ተጠርጣሪዎችን ጉዳይ በ559 የክስ መዝገቦች በማደራጀት 4 ሺህ 183 ተጠርጣሪዎች ላይ ክስ መመስረቱንም አስታውቀዋል፡፡መረጃ ከተጣራባቸው መካከል 2 ሺህ 351 ተጠርጣሪዎች በክልል፣ 3 ሺህ 314 በፌደራል እንዲሁም 63ቱ ደግሞ በሀረሪ ክልል ክስ ተመስርቶባቸዋል ነው የተባለው፡፡ከዚህ ባለፈ ግን 4 ሺህ 892 ምክር ተሰጥቷቸው ወደማህበረሰቡ የሚቀላቀሉ ይሆናል ተብሏል፡፡ | 1 |
9fd3b35f51b4241b95677ec29388acfc | 6208ba0126132ca5d19623a892de5644 | በአፍጋኒስታን አጥፍቶ ጠፊ ባደረሰው ፍንዳታ የሞትና የመቁሰል አደጋ ደረሰ | ምሥራቃዊ አፍጋኒስታን ውስጥ በደረሰ የአጥፍቶ ጠፊ ጥቃት ከሞቱት ሦስት ሰዎች አንዱ፣ ከፍተኛ የክፍለ ሀገር ባለሥልጣን መሆናቸው ተገለፀ።የምሥራቃዊ ናንጋርሃር ክፍለ ሀገር ዋና ከተማ በሆነችው ጃላላባድ የደረሰው ጥቃት ዒላማ ያደረገውና የገደለውም የሃይማኖታዊ ጉዳዮች ዳይሬክተርና የሀጂ መንፈሳዊ ጉዞ ክፍል ኃላፊ የሆኑትን አብዱላክ ዛሂር ሃቃኒንን እንደሆነም ባለሥልጣናት አስታውቀዋል።አንድ የክፍለ ሀገሩ መንግሥታዊ ቃል አቀባይ ለቪኦኤ እንደገለፀው፣ ጥቃቱን ያደረሰው አጥፍቶ ጠፊ፣ ወደ ባለሥልጣኑ ተሽከርካሪ በመጠጋት ነው ግድያውን የፈፀመው።የሃቃኒ ጠባቂ፣ ከሟቾቹ መካከል እንደበርና በፍንዳታው ሌሎች በርካታ ሰዎች እንደቆሰሉም ታውቋል። | 0 |
25b08d8d2710886623ce8a06bff3b6ff | b2b0c2e9626de672f7145e4c1a0d7861 | እንግሊዝ ከፈረንሳይ እና ከኔዘርላንድስ የሚገቡ ሰዎችን ለ14 ቀናት ወደ ለይቶ ማቆያ እንዲገቡ ልታስገድድ ነው | አዲስ አበባ፡- ኢትዮጵያን ጨምሮ በዓለም አቀፍ ደረጃ የተከሰተው የኮሮና ወረርሺኝ የአክሱም ሐውልት ጥገና ሥራን አስቸጋሪ እንዳደረገው የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን አስታወቀ። ለአክሱም ሐውልት ጥገና የተገዙ የጥገና ግብዓት ዕቃዎች በቅርቡ ወደ ሥፍራው እንደሚደርሱም ተገልጿል። የቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለሥልጣን ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ሙሉጌታ ፍስሃ በተለይም ለአዲስ ዘመን ጋዜጣ እንደገለጹት፤ ጥገናውን የሚያከናውነው የጣሊያኑ ላታንዚ ካምፓኒ ሲሆን ሥራውን ለመሥራት ውል የፈፀመውም በሁለት ነጥብ ስምንት ሚሊዮን ዩሮ ነው። ይሁንና በዓለም አቀፍ ደረጃ በተከሰተው የኮሮና ቫይረስ ወረርሺኝ ምክንያት የተጣለው የእንቅስቃሴ ገደብ ሥራውን ለማስቀጠል አስቸጋሪ አድርጎታል። የጥገና ሥራውን ለማከናወን የሚመጡት ባለሙያዎች ለ14 ቀናት ለይቶ ማቆያ ከመቆየታቸው ባለፈ ሥራውን ለመሥራት የወረርሽኙ አስከፊነት እስከሚቀንስም እየተጠበቀ ነው። ለአክሱም ሐውልት መዝመም ምክንያት የሆነው ከሥሩ ያለው የከርሰ ምድር ውሃ መስረግ መሆኑን የገለጹት ዶክተር ሙሉጌታ፤ የነገስታቱ መቃብርም ግድግዳው ከማርጀቱ በተጨማሪም ውሃ እየገባበት ነው። ይህንንም የአገር ውስጥና የጣሊያን ባለሙያዎች ለይተው ያስቀመጡት ሲሆን ጥናቱንም የተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባህል ድርጅት (ዩኔስኮ) አጽድቆታል። ሥራው ሲጀመር፤ በባለሙያዎች የሚከናወነው ተግባር የከርሰ ምድር ውሃውን ማውጣት እና በቀጣይም እንዳይገባበት አድርጎ ሐውልቱን ማቃናት ነው። በሌላም በኩል ለላሊበላ ቅርስ ጥገና ከፈረንሳይ ኤምባሲ ጋር በመሆን የጥገና ሥራ ለመጀመር እየተሰራ መሆኑን ዶክተር ሙሉጌታ ተናግረዋል። በስምምነቱም መሰረት ከጥገናው በፊት የምርምር ሥራ ይሰራል። የቅርሱ የመዋቅርና፣ የቅብ፣ የአለቶች ማርጀት፣ የመሰንጠቅ ደረጃው እና ሌሎች ባህሪያት እየተጠኑ ነው። በዚህም የሚመለከታቸው አካላት እየተሳተፉበት ነው። የምህንድስና፣ የኪነ ህንጻ (አርክቴክት)፣ የጂኦሎጂ እና የቅብ ባለሙያዎች በተደጋጋሚ እየተመላለሱ መረጃ ወስደው የመጀመሪያውን የምርምር ውጤት ከኮሮና ወረርሽኝ መከሰት በፊት አቅርበዋል። ቀጣይ የሚሆነው የተገኘውን የመጀመሪያ ዙር ጥናት ውጤት መሰረት በማድረግ ሥራውን መጀመር ነው። አዲስ ዘመን ሰኔ 13/2012 ዋለልኝ አየለ | 0 |
ac3419ec07b35692dcd11ba078e5e367 | 3069d000ba7ca0d321335fd7c2625f29 | መንግሥት የትራንስፖርት አቅርቦቱ ላይ አማራጮችን ማየት እንደሚገባው ተጠቆመ | የዋልድባ ገዳም መነኮሳትም ክሳቸው ተቋርጦ ይፈታሉ ተብሏልመንግሥት የፖለቲካ ምኅዳሩን ለማስፋትና አገራዊ መግባባት ለመፍጠር በማለት ታኅሳስ 25 ቀን 2010 ዓ.ም. ባስተላለፈው ውሳኔ መሠረት፣ ተጠርጣሪዎችንና ፍርደኞችን በሁለት ወራት ውስጥ እንደሚፈታ ያስቀመጠው የጊዜ ገደብ ሊጠናቀቅ ቀናት ቢቀሩትም እንደሚቀጥል ተጠቆመ፡፡ የክስ ጉዳያቸው በፍርድ ቤቶች በመታየት ላይ ያሉ ተጠርጣሪዎችና ወንጀል መፈጸማቸው ተረጋግጦባቸው የቅጣት ውሳኔ የተላለፉባቸው ፍርደኞች መንግሥት ያወጣውን መሥፈርት የሚያሟሉ ሆነው ከተገኙ፣ እስከ መጋቢት ወር መጀመርያ ድረስ እየተጣራ እንደሚለቀቁ የፌዴራል ጠቅላይ ዓቃቤ ሕግ አቶ ጌታቸው አምባዬ መግለጻቸው ይታወሳል፡፡ በዚህም መሠረት በመላው አገሪቱ ማረሚያ ቤቶች ከሚገኙ ተጠርጣሪዎችና ፍርደኞች መካከል ከሰባት ሺሕ በላይ የሚሆኑት ክሳቸው መቋረጡና በይቅርታ መለቀቃቸው ይታወሳል፡፡ነገር ግን በቀጣይም የክስ ሒደታቸው እየታየ የሚቋረጥላቸውና በይቅርታ የሚፈቱ እንዳሉ የሪፖርተር ምንጮች አረጋግጠው፣ ምንም እንኳን በመንግሥት በኩል የተነገረው የመፍቻ የሁለት ወራት ጊዜ ሊጠናቀቅ ቀናት የቀሩት ቢሆንም፣ ሊቀጥል እንደሚችል አስረድተዋል፡፡ የሪፖርተር ምንጮች እንደገለጹት፣ በሽብር ተግባር ወንጀል ክስ የተመሠረተባቸው የዋልድባ ገዳም ሁለት መነኮሳትን ጨምሮ ሌሎች ተከሳሾችም ክስ እንደሚቋረጥና ተፈርዶባቸው በእስር ላይ የሚገኙም በይቅርታ እንደሚፈቱ አስረድተዋል፡፡ መንግሥት የሰጠው የጊዜ ገደብ ግን ቅዳሜ መጋቢት 1 ቀን 2010 ዓ.ም. እንደሚያበቃ ታውቋል፡፡ | 0 |
0cf53f685287bf867528130528f41f16 | 8d3f7909d14420063d10d97e68144e59 | መሐመድ ናስር ዳግም ቡድኑን ተቀላቅሏል | ከፔትሮጀክት ጋር ስኬታማ ሶስት ዓመታቶችን ያሳለፈው ኢትዮጵያዊው አማካይ ሽመልስ በቀለ ወደ ሌላኛው የግብፅ ክለብ ምስር አል ማቃሳ በሶስት አመት የውል ስምምነት ተቀላቅሏል፡፡በሀዋሳ ከተማ የእግር ኳስ ህይወቱን የጀመረውና ቀጥሎም በቅዱስ ጊዮርጊስ መጫወት የቻለው የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን የአማካይ ስፍራ ተጫዋቹ ሽመልስ በቀለ ከኢትዮጵያ ውጭ በመውጣት በሊቢያው ክለብ አል አህሊ ትሪፖሊ ካመራ በኋላ ብዙም ሳይቆይ ወደ ሱዳን አምርቶ ለኤልሜሪክ ተሰልፎ ተጫውቷል። ቀጥሎ ወደ ግብፅ በማቅናት ያለፉትን ሶስት ዓመታት በፔትሮጄት ክለብ ውስጥ በአምበልነት ቡድኑን እየመራ ወሳኝ የሚባሉ ግቦችን ለክለቡ ሲያስቆጥርም ቆይቷል። ስኬታማ ዓመታትን በፔትሮጀክት ያሳለፈው ኢትዮጵያዊው የመሀል ሜዳ ተጫዋች ሽመልስ ቀሪ የሶስት ወር ኮንትራት ከፔትሮጀክት ጋር ቢቀረውም በስምምነት ወደ ሌላኛው የግብፅ ክለብ ምስር ኤልማቃሳ በሶስት ዓመት ውል በይፋ ትላንት ተቀላቅሏል፡፡ ተጫዋቹ የተሳካ የውድድር ዓመት ከአዲሱ ክለቡ ጋር ለማሳካት እንደሚጥርም ለሶከር ኢትዮጵያ ተናግሯል፡፡የሽመልሱ አዲሱ ክለብ ምስር ኤልማቃሳ ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት መከላከያን በኮንፌዴሬሽን ዋንጫ መግጠሙ ይታወሳል፡፡ | 0 |
3f18a6ac42c89a8ce4ce06b71fd23968 | 264696b1a7cca11b3a9474932cb24af5 | የሰብአዊ መብቶች ተሟጋቹ ኦባንግ ሜቶ በኢትዮጵያ ወቅታዊ ሁኔታ ላይ | የኢትዮጵያ ሰብአዊ መብቶች ጉባኤ፤ የአርቲስት ሃጫሉ ሁንዴሳ ግድያን ተከትሎ በተፈጠረው ሁከትና ግርግር በኦሮሚያ የደረሰውን የሰብአዊ ጉዳት የሚመረምር ቡድን ከሣምንቱ አጋማሽ ጀምሮ ማሠማራቱን ለአዲስ አድማስ አስታውቋል:: ተቋሙ ሁከትና ግርግር በተፈጠረባቸውና ጉዳት በደረሰባቸው ሁሉም የኦሮሚያ አካባቢዎች የምርመራ ቡድን ማሰማራቱን አመልክቷል፡፡ በምርመራው የሚገኙ ውጤቶችን ከዓለማቀፍ የሰብአዊ መብት ድንጋጌዎች አንፃር በመመዘን የተፈፀመው ድርጊት ምንድን ነው? ምን ያህል ጉዳት አጋጥሟል? መንግስት የወሰደው እርምጃስ ምንድን ነው? እነማን በድርጊቱ ተሳትፈዋል? የሚለውን የመለየት ተግባር እንደሚከናወን ታውቋል፡፡ | 0 |
db97d7a0013aa3a7eaafcbb877b34307 | 6c4c5aae6b3641a945682709e34ad176 | ፑቲን ለሚኒስትሮቻቸው የአዲስ ዓመት እረፍት የለም አሉ | በፕሬዚዳንት ቭላዲሚር ፑቲን ላይ አድማ አቀነባብረዋል ተብለው ባለፈው ወር የታሰሩት ሩስያዊው ተቃዋሚ መሪ አሌክሲ ናቫልኒ፣ ከ30 ቀናት እስር በኋላ በዛሬው ዕለት መፈታታቸው ተገለፀ።«ከ30 ቀናት የሥራ ጉዞ በኋላ እነሆ ተመልሻለሁ» ሲሉ ትዊት ያደረጉት ናቫልኒ፣ “ነፃ በመሆኔ ተደስቻለሁም” ብለዋል።ናቫልኒና በመቶዎች የሚቆጠሩ ደጋፊዎቻቸው የታሰሩት ባለፈው ወር ሲሆን፣ ይህም ፕሬዚዳንት ፑቲንን ለሌላ ሥድስት ዓመት በሥልጣን ለማቆየት የሚያስችለው ሥነ ሥርዓት ሞስኮ ውስጥ በሚካሄድበት ዋዜማ መሆኑ ነው። | 0 |
07934008b29a32eec6eaacfc7460d65c | b4cf8a0868b3a0185a58bf88aa4ca3e0 | በፍቅርና በሰላም ስንደመር ዛሬን ብቻ ሳይሆን ነገን መስራት እንችላለን —ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ | መንግስት የአዲስ አበባን ወጣት ለይቶ የማጥቃትና የማሰር ፍላጎት የለውም ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ገልጸዋል፡፡የአዲስ አበባ ወጣት ስራ ሳይኖረውና በችግር ውስጥ ሆኖ እንኳን አሁን ላለው ለውጥ ትልቅ መስዋዕትነት የከፈለ እንደሆነ ያስታወሱት ዶክተር አብይ ለዚህ ተግባሩ ምስጋና ብቻ ሳይሆን የመሪነት ሚና ሊሰጠው ይገባል ብለዋል፡፡ይሁን እንጂ አዲስ አበባን ማዕከል አድርጎ በመበጥበጥ ብቻ ነው መንግስትን ማዳከም የሚቻለው በሚል አስተሳሰብ ሰላሙን የማይፈልጉ አካላት በዚሁ ከተማ ውስጥ ከፍተኛ ገንዘብ መድበው ለማተራመስ ጥረት ማድረጋቸውን አውስተዋል፡፡በዚህም መሠረት ምን እየተካሄደ እንደሆነ እንኳን በውል ያልተገነዘቡ አንዳንድ ወጣቶች በትንንሽ ገንዘብ ተደልለው ወደዚህ ተግባር መሠማራታውንም ጠቅላይ ሚንስትሩ ጠቁመዋል፡፡በመሆኑም ሃገርን የማተራመስ አጀንዳውን በጥልቀት ሳይረዱ ወደዚህ እኩይ ተግባር የተሰማሩ ወጣቶችን የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና እየሰጠን ሲሆን ማስረጃ የተገኘባቸውን አካላት ለህግ የማቅረብ ስራ እየተሰራ ነው ብለዋል፡፡ዜጎች ሁሉ እኩል ናቸው፣ አንደኛና ሁለተኛ ዜጋ የሚባል ነገር የለም ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወንጀለኞች ከየትኛውም ብሄርና ከማንኛውም የሥልጣን ደረጃ ቢመጡም በህግ ከመጠየቅ አያመልጡም ብለዋል፡፡ወንጀለኞቹ ትልቅ አቅም የፈጠሩ በመሆናቸው ወንጀል ሲሰሩ ማስረጃው እንዳይገኝ አድርገው ስለሆነ ለህግ የማቅረቡን ስራ ቀላል እንዳይሆን ማድረጋቸውንም ጠቁመዋል፡፡ | 0 |
b004455c57495922b6d57d760c2527d7 | 3927dfe2f8612976d9116d8ba9a9c826 | የአዲስ አበባ ንግድ ምክር ቤት ባለአደራ ቦርድ ሥራ ጀመረ | አዲስ አበባ፣ ጥር 22፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በመዲናዋ የተማሪዎች ምገባ መርሃ ግብርን በዘላቂነት ለማስቀጠል ቁርጠኛ አቋም እንዳለው የተማሪዎች ምገባ ኤጀንሲ ቦርድ አስታውቋል።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት ባሳለፍነው ሳምንት የተማሪዎች ምገባ ኤጀንሲ ቦርድ እንዲቋቋም መወሰኑ ይታወቃል።የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ ወይዘሮ ፍሬዓለም ሽባባው ከፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ጋር ባደረጉት ቆይታ፥መርሃ ግብሩ ተማሪዎችን ከማገዝ ባሻገር በከተማዋ ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃ ላይ አዎንታዊ አስተዋጽኦ እንደሚያበረክት ተናግረዋል።ከዚህ ባሻገር በአዲስ አበባ ከተማ እና ዙሪያ በሚገኙ አርሶ አደሮች መካከል የገበያ ትስስር ለመፍጠር ያስችላል ነው የተባለው።መርሃ ግብሩ በሀገር አቀፍ ደራጃ ተግባራዊ መደረግ እንደሚገባው የገለጹት ወይዘሮ ፍሬዓለም ለዚህም የሚመለከታቸው አካላት በቅንጅት ሊሰሩ ይገባል ነው ያሉት።በዚህ መሰረትም ፖለቲከኞች፣ ባለሃብቶች፣ ወላጆች እና ሌሎች ባለድርሻ አካላት ለመርሃ ግብሩ ቀጣይነት እና መሻሻል የበኩላቸውን አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱ ጥሪ አቅርበዋል።ቦርዱ መርሃ ግብሩን በዘላቂነት በማሻሻል ለመላ ሀገሪቱ የሚሆን ተሞክሮ የመቀመር እቅድ እንዳለው ነው ምክትል ሰብሳቢዋ የተናገሩት።የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በመርሃ ግብሩ በዘንድሮው ዓመት ለ600 ሺህ ተማሪዎች ዩኒፎርምን ጨምሮ የተለያዩ የትምህርት መርጃ ቁሳቁሶችን ያቀረበ ሲሆን፥ 300 ሺህ ተማሪዎችን ደግሞ የትምህርት ቤት ምገባ መርሃ ግብር ተጠቃሚ አድርጓል።በትዕግስት ስለሺ | 0 |
6bd1299f9ccb622ea3accb9800a676ec | 247735503979fb8938dc9f697b08ed39 | ስሑል ሽረ አይቮሪኮስታዊውን ተጫዋች አስፈረመ | ባለፈው ክረምት ስሑል ሽረን የተቀላቀለው መድሀኔ ብርሃኔ ከቡድኑ ጋር በስምምነት ተለያይቶ ወደ ሀዲያ ሆሳዕና አምርቷል።ከደደቢት ጋር የተሳካ ዓመት ካሳለፈ በኋላ በክረምቱ ዝውውር መስኮት የመጨረሻ ቀን ስሑል ሽረን የተቀላቀለው ሁለገቡ መድሀኔ ብርሀኔ በስሑል ሽረ ቆይታው መስመር ተከላካይነት ፣ በመስመር ተጫዋችነት እና በፊት አጥቂነት መጫወት የቻለ ሲሆን በሊጉ የመጀመርያ ሳምንታት ቡድኑን በቋሚነት ቢያገለግልም ቆይቶ ባልታወቀ ምክንያት ቡድኑን ማገልገል አልቻለም።ከደደቢት ታዳጊ ቡድን አድጎ እስከ ባለፈው ዓመት ከሰማያዊዎቹ ጋር ቆይታ የነበረውና በመሐል ለቢሾፍተለ አውቶሞቲቭ የተጫወተው ይህ ተጫዋች ባስገባው የልቀቁኝ ደብዳቤ መሰረት ከቡድኑ ጋር በስምምነት ተለያይቶ ዛሬ አራተኛ የክለቡ ፈራሚ በመሆን ሀዲያን ተቀላቅሏል።ሀዲያ ሆሳዕና ከመድሃኔ በፊት ሳሊፍ ፎፋና፣ ተስፋዬ አለባቸው እና ቢኒያም ሲራጅን ማስፈረሙ ይታወቃል።©ሶከር ኢትዮጵያ | 0 |
f7dfb89e9c3253461257bad33371a087 | f7dfb89e9c3253461257bad33371a087 | የዴሞክራቲክ ኰንጎ መሪ ለተቃዋሚዎች ምሕረት ሰጡ | ፕሬዚደንት ጆሴፍ ካቢላ በቅርቡ ያወጁትን የሰላም ጥሪ፣ የBDK ንቅናቄ መሪ Ne Muanda Nsemi ደግፈውና ምሕረትም ጠይቀው እንደነበር ታውቋል። በዚሁ መሠረት ነው ፕሬዚደንት ካቢላ፣ ዕድሜያቸው ከ70 ዓመት በላይ ለሆኑ የንቅናቄው እስረኞ ምህረት ያደረጉት።ቢ ዲ ኬ (BDK) እራሱን እንደ ሃይማኖታዊ ንቅናቄ አድርጎ ነው የሚቆጥረው። ዓላማውም፣ ደቡባዊ ኰንጎ ዴሞክራቲክ ውስጥ ላለችው የባስ ኮንጎ (Bas Congo) ክልል፣ የራስ አስተዳደር እንዱመሰረት ነው። መሪውም ኔ ሟንዳ ንሰሚ (Ne Muanda Nsemi) ወደ ንቅናቄው የገቡት ደግሞ ራዕይ ተገልጦላቸው እንደሆነ ያምናሉ።እናም ፕሬዚደንት ካቢላ በአዲሱ ዓመት ዋዜማ ባስተላለፉት ብሔራዊ ጥሪ፣ ዛሬ በጀመረው በአዲሱ የ2016 ዓም የፖለቲካ ድርድር ለመጀመር መወሰናቸውን ይፋ አደረጉ።ሆኖም አንዳንድ ተተቃዋሚዎች፣ የካቢላን የሰላም ጥሪም ሆነ የምህረት ዓዋጅ፣ የመደለያና የሥልጣን ማራዘሚያ አድርገው እንደሚያዩት፣ የፖለቲካ ተንታኞች ይናገራሉ።አዲሱ አበበ ያቀናበረውን ዘገባ ከድምጽ ፋይሉ ያድምጡ። | 1 |
6ef7e60846ded4aa0c1544a2d75521e4 | c90ce10ed3ebcfd7c182b102584bb7f6 | ጠ/ሚ ዐቢይ ያገኙት የኖቤል የሰላም ሽልማት ሜዳሊያና ዲፕሎማ ቅጂ በሰላም ሚኒስቴር ተቀመጠ | በጦርነት ተጎጂ የሆኑ ህፃናትን መታደግ በሚቻልበት ሁኔታ ላይ በሚመክረው ዉይይት ባለፉት 20 አመታት በጦርነት ምክንያት 5 ሚሊየን ህፃናት በሞቱባት አፍሪካ የህፃናት መብት እንዲከበርና ችግሩ እልባት እንዲያገኝ ተጠይቋል፡፡በዉይይት መድረኩ ከኢትዮጵያ፣ ማሊ፣ ደቡብ ሱዳን፣ ናይጄሪያና ኮንጎ የተገኙ ህፃናት ተሳትፈዋል፡፡
በዉይይት መድረኩ ላይ የተገኙት የሴቭ ዘ ችልድረን ዳይሬክተር ያ ቬል አገራት የህፃናትን መብት ለመጠበቅ የገቧቸዉን አለምአቀፍ ስምምነቶች ሊያከብሩ ይገባል ብለዋል፡፡የአፍሪካ ህብረት ምክትል ሊቀመንበር አምባሳደር ቶማስ ክዌሲ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ያገኙት የሰላም የኖቤል ሽልማት ለሰላም ያደረጉት ጥረት ማሳያ እንደሆነ ተናግረዉ ለአህጉሩ ትልቅ መነቃቃትን ይፈጥራል ብለዋል፡፡በአፍሪካ የመሳሪያ ድምፅ እንዳይሰማ የተደረሰዉ ስምምነት ተግባራዊ እንዲሆን እየተሰራ ነዉ ብለዋል፡፡
የሴቶች ህፃናትና ወጣቶች ሚኒስትር ዴኤታ ወ/ሮ አለሚቱ ዑመድ በበኩላቸዉ ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ በአፍሪካ ሰላም እንዲሰፍን እየሰሩ መሆኑንና የኖቤል ሽልማቱም ይህን እንደሚያሳይ ተናገረዋል፡፡በኢትዮጵያ ባለፉት ጥቂት አመታት በነበረዉ የዉስጥ መፈናቀል ችግር የደረሰባቸዉን ህፃናት መልሶ ለማቋቋም እየተሰራ መሆኑንም ጠቁመዋል፡፡ | 0 |
02ad439643063810e77aa3bdd510691e | 47b1660c75d66bdc7765b747fc8b854b | ታቦት ተሸካሚው አርበኛ | የኢትዮጵያ ታላቁ ሕዳሴ ግድብ ግንባታ በ2003 ዓ.ም ተጀመረ።• ግድቡ ሲጠናቀቅ ከ 74 ቢሊዮን ኪዩቢክ ሜትር ውሃ በላይ ቦታ ይይዛል።• የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ ለመሙላት የሚወስድባት ጊዜ እስከ ሰባት አመት ነው።• በሚመጣው ክረምት የውሃ ሙሌት ይጀ መራል። •ታህሳስ 2013 ዓ.ም የመጀመሪያዎቹ ሁለት ተርባይኖች ኃይል ማመንጨት ይጀምራሉ። እያንዳንዳቸው የኃይል ማመንጫ ተርባይን 375 ሜጋዋት በጠቅላላው 750 ሜጋ ዋት ኃይል ለማመንጨ ይችላሉ።• በእያንዳንዱ ኢትዮጵያውያን የገንዘብ መዋጮ የሚገነባና የሁሉም ዜጋ አሻራ ያረፈበት ነው። • ግድቡ ሲጠናቀቅ 6ሺህ ዋት የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም ይኖረዋል።• በርካታ ሕዝብ የኤሌክትሪክ ኃይል እንደልብ በማያገኝባት ኢትዮጵያ ግድቡ ሲጠናቀቅ ዘርፈ ብዙ ጥቅሞችን ይሰጣል። • ከዚህ ባለፈም እያደገ ለመጣው የማኑፋ ክቸሪንግ ዘርፍ ትልቅ እፎይታን የሚሰጥ ይሆናል።• ኢትዮጵያ ግድቡ ሙሉ በሙሉ ኃይል ማመንጨት ሲጀምርላት ለጎረቤት ሀገራት ኮረንቲ መሸጥ ትችላለች። በተለይ ደግሞ ሱዳን፣ ደቡብ ሱዳን፣ ኤርትራና ጂቡቲ ከሕዳሴው ግድብ ጥቅም የሚገኙ ሀገሮች ናቸው።• ታላቁ ህዳሴ ግድብ አጠቃላይ የግንባታ ሒደት 72 በመቶ ደርሷል።• በአሁኑ ወቅት የኤሌክትሮ ሜካኒካል ሥራዎቹ ከ42.3 በመቶ በላይ ተጠናቀዋል።•የሲቪል ስትራክቸር የግንባታ ሒደትም ከ20 በመቶ በላይ አፈጻጸም አስመዝግቧል።•መጋቢት 24 ቀን 2012 ዓ.ም ዘጠነኛ አመት የምስረታ በዓሉን ያከብራል።አዲስ ዘመን መጋቢት 20 ቀን 2012 ዓ.ም | 0 |
d182a37a36ea19919205c2aa2c15323a | d79d49719874bace7683693ba12e7fad | የኢትዮ- ሱዳን የድንበር ጉዳይ እንዲጦዝ የፈለጉት የኢትዮጵያ ጠላቶች ናቸው – አምባሳደር ዲና | የሱዳን ታጣቂዎችና ሚሊሻዎች ከሰሞኑ የኢትዮጵያን ድንበር አልፈው ጥቃት መፈፀማቸውን የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ ገለጹ፡፡ሚሊሻዎቹ እና ታጣቂዎቹ የገበሬዎችን ማሳ በመዝረፍ እና በማፈናቀል በርካታ ህገ ወጥ ድርጊት መፈጸማቸውን አምባሳደር ዲና ከዋልታ ጋር በነበራቸው ቆይታ ገልጸዋል፡፡የኢትዮጵያ መንግስት ጉዳዩን በሰላማዊ መንገድ ለመፍታት ከሱዳን አመራሮች ጋር እየተነጋገረ መሆኑን የገለጹት አምባሳደር ዲና፣ በሀለቱ ሀገራት መካከል ልዩነትን ለመፍጠር የሚፈልጉ አካላትና ወደ ሱዳን የሸሸው የጁንታው ቡድን ሁኔታው እንዲባባስ እየሰራ መሆኑን ጠቁመዋል፡፡የመሬት ይዞታ ባለቤትነት ጥያቄ በአንዳንድ የሱዳን ፖለቲከኞችም ይስተዋላል ያሉት ቃልአቀባዩ፣ ድርጊቱን በመደገፍ በሱዳን የሚገኙ መገናኛ ብዙኃንም ሲያራግቡት መቆየታቸውን አንስዋል፡፡ከሰሞኑ በሱዳን በሚኖሩ ኢትዮጵያውያን ላይም ብሔርን መነሻ ያደረገ ማጎሳቆል እንደደረሰባቸውም ተናግረዋል፡፡ኢትዮጵያ በህግ ማስከበር ሂደት ውስጥ መሆኗን እንደ መልካም አጋጣሚ በመጠቀም የሀገሪቱን ሰላም ለማደፍረስ የሚጥሩ አካላት ሁኔታዎችን ለማባባስ እየሰሩ መሆናቸውም ተነግሯል፡፡(በመስከረም ቸርነት) | 0 |
8b9a1843006506eb811507b8cb0b2f0b | a6e60060aca30f41e786ed57195efe26 | የባለድርሻ አካላት ቅንጅት መጓደል ለነዳጅ እጥረት መንስኤ ነው ተባለ | የአለም የነዳጅ ዋጋ መቀነስ በዚሁ የሚቀጥል ከሆነ ኢትዮጵያ የምታካሂዳቸውን ግዙፍ የልማት ፕሮጀክቶች ለማቀላጠፍ እንደሚያግዝ የንግድ ሚኒስትር ዴኤታው አቶ አሊ ሲራጅ ለፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬት ተናግረዋል።ሃገሪቱ ለነዳጅ ግዢ የምታወጣው ገንዘብ ከወጪ ንግድ ገቢዋ እንደሚልቅ ያነሱት ሚኒስትር ዴኤታው፥ ላለፉት ዓመታትም ለነዳጅ ዋጋ ድጎማ መንግስት 6 ቢሊየን ብር ማውጣቱንም ጠቁመዋል።በዚህም ምክንያቶች ሃገሪቱ ለግዙፍ ፕሮጀክቶች ማስፈፀሚያ የሚውለውን የውጭ ምንዛሪ ለግዢ ታውለው እንደነበር ነው የተናገሩት።ሆኖም በአሁኑ ወቀት የታየው የነዳጅ ዋጋ ቅናሽ በዚሁ ከቀጠለ መንግስት ያሉትን ፕሮጀክቶች የማስፈፀም አቅሙ ይጎለብታል ተብሏል።ጣቢያችን ያናጋገራቸው የኢኮኖሚ አማካሪ፣ አቶ ዘመዴነህ ንጋቱም የነዳጅ ዋጋ አሁን ባለበት ለአንድ አመት ተኩል ከቀጠለ ሃገሪቱ ለነዳጅ ታወጣ የነበረውን 1 ቢሊየን ዶላር ማዳን ትችላለች ብለዋል።ይህም ከሌሎች የውጪ ምንዛሪ ገቢዎች ጋር ተዳምሮ ለሃገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት ከፍተኛ አስተዋፅኦ ያበረክታል መባሉን ኤፍ ቢ ሲ ዘግቧል። | 0 |
08dd567a7a374116d143174677c1ffe2 | 08dd567a7a374116d143174677c1ffe2 | መቐለ ከተማ 5ኛ ተጫዋቹን አስፈርሟል | ገብረመድህን ኃይሌን አሰልጣኝ አድርጎ የመረጠው መቐለ ከተማ በዝውውር መስኮቱ በስፋት እየተንቀሳቀሰ ይገኛል። ያሬድ ሀስንንም የክለቡ 5ኛ አዲስ ፈራሚ አድርጎ ወደ ቡድኑ ቀላቅሏል።የቀድሞው የኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች ብሔራዊ ቡድን አማካይ ከወልዲያ ያለፉት ሶስት የውድድር ዘመናት ቆይታ በኋላ በመልቀቅ የሰሜን ኢትዮጵያውን ክለብ በአንድ ዓመት ውል ተቀላቅሏል። የግራ እግር ተጫዋቹ ያሬድ ከአማካይነት በተጨማሪ በመስመር ተከላካይነት መጫወት የሚችል ተጫዋች ነው።መቐለ እስካሁን አምስት ተጫዋቾችን ሲያስፈርም ከክለቡ ጋር የማይቀጥሉ ተጫዋቾችንም እየለየ ይገኛል። ሐብታሙ ተከስተ እና ጋቶች ፓኖም ወደ ሌሎች ክለቦች ሲያመሩ በውድድር ዓመቱ አጋማሽ ክለቡን ተቀላቅለው ብዙም ግልጋሎት ያልሰጡት ካርሎስ ዳምጠው፣ እያሱ ተስፋዬ እና ቶክ ጀምስ ከክለቡ ጋር የማይቀጥሉ ተጨዋቾች መሆናቸው ተገልጿል። | 1 |
94ca7dd1501f2f3a4c128663295c87e6 | dfe169f56730312dca4b8a4b621a9b9d | የኢፌዴሪ አየር ኃይል ዋና አዛዥ ሜጀር ጀኔራል ይልማ መርዳሳ የምዕራብ አየር ምድብን ጎበኙ | አዲስ አበባ፣ ጥቅምት 12፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የልዩ ዘመቻዎች ሀይል ስልጠና በቀጣይ በሀገር ላይ ሊመጡ የሚችሉ ችግሮችን አስቀድሞ ለመመከት የሚያስችል መሆኑን የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት የልዩ ዘመቻዎች ኃይል ዋና አዛዥ ሜጀር ጀነራል ሹማ አብደታ ተናገሩ።የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት የልዩ ዘመቻዎች ኃይል ማዘዣ በአምስት ሻለቃ ያሰለጠናቸውን የኮማንዶ አባላትን የፊታችን ቅዳሜ ያስመርቃል።ስልጠናውን የወሰዱት የኮማንዶ አባላት ልዩ ልዩ ግዳጆችን የሚወጡ መሆናቸው ተገልጿል።የኢፌዴሪ መከላከያ ሰራዊት የልዩ ዘመቻ ኃይል ዋና አዛዥ ሜጀር ጀነራል ሹማ አብደታ ÷ የልዩ ዘመቻዎች ኃይል ስልጠና በአገር ላይ ስጋት ሊሆኑ የሚችሉ ችግሮችን አስቀድሞ ለመመከት የሚያስችል ነው ብለዋል።ስልጠናው እንደ ሀገር በቀጣይ ሊመጡ የሚችሉ ችግሮችን እንዴት መከላከልና መወጣት እንደሚቻል በተግባር የታየበት ነው ሲሉም አስረድተዋል።የልዩ ዘመቻዎች ኃይል ስልጠናው ተፈጥሯዊም ሆነ ሰው ሰራሽ አደጋን በመቋቋም ግዳጅን መወጣት የሚያስችል መሆኑንም ነው የገለጹት።የአለም ስጋት እየሆነ የመጣውን የሽብር ጥቃት አስቀድሞ ለመከላከል ብሎም በከተሞችና ምቹ ባልሆኑ አካባቢዎች ተልዕኮን ለመወጣት እንደሚያስችልም ዋና አዛዡ አስታውቀዋል።የኢፌዴሪ የመከላከያ ሰራዊት “የሀገር ዋልታ፣ የህዝብ አለኝታ” መሆኑን አንስተው÷ሠላምንና የሀገርን ደህንነት ለማስጠበቅ የሚሰራ ኃይል መሆኑንም ተናግረዋል።በልዩ ዘመቻዎች ኃይል ማዘዣ የተሰጠው ስልጠና አንድ ሻለቃ ኮማንዶ የሪፐብሊካን ጋርድ፣ ሁለት ሻለቃ ልዩ ኃይል ፣ አንድ ሻለቃ የጸረ ሽብር ልዩ ኃይል እንዲሁም አንድ ሻለቃ የፌደራል ፓሊስ ኮማንዶን የያዘ ነው ብለዋል።በነገው እለትም በልዩ ዘመቻዎች ሀይል የሰለጠኑ የአየር ወለድ ኮማንዶ አባላት የተለያዩ ትርኢቶችን ያሳያሉ መባሉን ኢዜአ ዘግቧል።
የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ። | 0 |
4e72d68e60617533ccf1679e2a68d602 | f58637b9438ed6e8809d741a8330c64d | የለንደኑ “ግሬንፌል”የመኖሪያ ሕንፃ ቃጠሎ በኋላ አደጋዎችን ለመከላከል በብሄራዊ ደረጃ ምርመራ ተጀምሯል | የቦሌ ክፍለ ከተማ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ጽሕፈት ቤት የኅብረት ሥራ ማኅበራት መኖሪያ ቤት የመስተንግዶ ባለሙያና የኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ የኅብረት ሥራ ማኅበራት ማስፋፊያ ቡድን መሪን ጨምሮ፣ ስድስት ግለሰቦች በሙስና ተጠርጥረው ክስ ተመሠረተባቸው::ተከሳሾቹ በጥቅም በመተሳሰር ቀራኒዮ ተራራ ቁጥር 2/33 የጋራ ሕንፃ መኖሪያ ቤት ኃላፊነቱ የተወሰነ የኅብረት ሥራ ማኅበር አባላት ሲተካኩ፣ የማኅበሩን ሕጋዊነት ሳያረጋግጡ ማፅደቃቸውን ክሱ ይጠቁማል:: በመሆኑም የማኅበሩ ሕጋዊነት ሳይረጋገጥ የመተካካት ሥራ እንዲፈጸም በማድረግና የመንግሥትን ይዞታ ያላግባብ በማስተላለፍ፣ በመንግሥት ላይ የ3,914,949 ብር ጉዳት ማድረሳቸውን፣ የፌዴራል የሥነ ምግባርና ፀረ ሙስና ኮሚሽን ክስ ያስረዳል::ተጠርጣሪ ተከሳሾቹ የቦሌ ክፍለ ከተማ ንግድና ኢንዱስትሪ ልማት ጽሕፈት ቤት የኅብረት ሥራ ማኅበራት መኖሪያ ቤት የመስተንግዶ ባለሙያ አቶ ብርሃነ ግርማይ፣ በግል ሥራ የሚተዳደሩት አቶ መህዲ ሰፋና አቶ ዓለማየሁ ወልደየስ፣ የኅብረት ሥራ ከፍተኛ አደራጅና ምዝገባ ባለሙያ አቶ ተወልደ ገብረ ሚካኤል፣ በኮልፌ ቀራኒዮ ክፍለ ከተማ የኅብረት ሥራ ማኅበራት ማስፋፊያ ቡድን መሪ አቶ ተሞገስ ወልደ አምላክና አቶ ጌታቸው ድንቁ ናቸው::ተከሳሾቹ በተጠቀሰው የጋራ መኖሪያ ሕንፃ የመኖሪያ ቤት ማኅበር መሥራች አባላቱ በወቅቱ ሲደራጁ የአዲስ አበባ ነዋሪነታቸውን የሚገልጽ መታወቂያ በወቅቱ መዘጋጀት ሲገባው፣ በተለያዩ ጊዜያት መታወቂያ በመስጠት ሕገወጥ ተግባር መፈጸማቸውን ክሱ ያብራራል:: በመሆኑም ተጠርጣሪዎቹ ኃላፊነታቸውን ወደ ጎን በማለትና ሥልጣናቸውን ያላግባብ በመገልገል በመንግሥት ላይ ጉዳት በማድረሳቸው፣ በሙስና ወንጀል መከሰሳቸውን ክሱ ያስረዳል:: | 0 |
ea5a054a10dbb551353e3cc778db7c9c | ea5a054a10dbb551353e3cc778db7c9c | የገና በዓል በክርስትና እምነት ተከታዮች ዘንድ በመላው ኢትዮጵያ ተከበረ | በዓሉን በማስመልከትም የተለያዩ የኃይማኖት መሪዎች የመልካም በዓል ምኞታቸውን አስተላልፈዋል።የእምነቱ ተከታዮች በዓሉን የተቸግሩትን በማሰብ ሊከበር እንደሚገባ የኃይማኖቱ አባቶች መክረዋል።የእየሱስ ክርስቶስ ልደት ዋዜማ በየአብያተ ክርስቲያናቱ በተለያዩ መንፈሳዊ ስነስርአቶች ከትላንት በስተያ ተከብሯል፡፡የኃይማኖት መሪዎቹ የየእምነቱ ተከታዮች በዓሉን በመተሳሰብ እና በመፈቃቀር እንዲሁም በድርቅ ምክንያት ለምግብ እጥረት የተጋለጡ ወገኖችን በመርዳትና በመደገፍ ሊያከብሩት ይገባል ሲሉ መልዕክታቸውን አስተላልፈዋል።የገና በዓል በላሊበላ ከተማ በርካታ አማኒያንና ከውጭ የተገኙ ቱሪስቶች በተገኙበት ከመላው ኢትዮጵያ በልዩ ሁኔታ በድምቀት ተከብሯል።በገና በዓል ዕለት የገና ጨዋታም የዕለቱ ማደመቂያ መሆኑ ይታወቃል።(ኢቢኮ) | 1 |
b990d75a32da74d73cb5155d78b38925 | 15613b77924baffbfc807f13bc8b6222 | ተመድ በዓለም ዙሪያ ለሠላሳ ሦስት ሃገሮች የገንዘብ ድጋፍ ጠየቀ | ኤልኒኖ የተሰኘው የአየር ፀባይ ክስተት ባስከተለው ድርቅ ሳቢያ ለተጎዱ 9.7 ሚሊዮን ዜጎች ዕርዳታ የሚውል እ.ኤ.አ. በ2017 ብቻ 900 ሚሊዮን ዶላር እንደሚያስፈልግ፣ የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት (ተመድ) የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት አስታወቀ፡፡ጽሕፈት ቤቱ ሰኞ ታኅሳስ 3 ቀን 2009 ዓ.ም. ባወጣው መግለጫ የሚያስፈልገው የገንዘብ መጠን እ.ኤ.አ. ከ2016 ሲነፃፀር በ44 በመቶ እንደሚቀንስ የገለጸ ቢሆንም፣ የኢትዮጵያ መንግሥትና አጋር ድርጅቶች በጋራ ባካሄዱት ዳሰሳ በአገሪቱ ምሥራቅና ደቡብ አካባቢዎች አዲስ የድርቅ ምልክቶች መታየታቸውን ጠቁሟል፡፡ ከ5.6 ሚሊዮን በላይ ዜጎች የምግብ ዕርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው ገልጾ፣ 1.2 ሚሊዮን ሕፃናት፣ ነፍሰ ጡሮችና አጥቢ እናቶች ተጨማሪ ምግብ እንደሚያስፈልጋቸው ጽሕፈት ቤቱ አስታውቋል፡፡በኤልኒኖ አማካይነት በተከሰተው ድርቅና በተጓዳኝ በተከሰተው የተጠናከረ ጎርፍ በበሽታዎችና በተቋረጡ መሠረታዊ አገልግሎቶች ሳቢያ 9.7 ሚሊዮን ያህል ዜጎች ሕይወት መቃወሱ ተገልጿል፡፡ ከ9.2 ሚሊዮን በላይ ዜጎች ንፁህ የመጠጥ ውኃ እንደማያገኙ፣ 2.4 ሚሊዮን ቤተሰቦች ለከብቶቻቸው የመኖና የጤና ድጋፍ እንደሚፈልጉ ተገምቷል፡፡ እ.ኤ.አ. በ2017 ብቻ 300,000 ያህል ሕፃናት የከፋ የተመጣጠነ ምግብ እጥረት እንደሚገጥማቸው አጋር ድርጅቶች መተንበያቸውን ጽሕፈት ቤቱ አስታውቋል፡፡እ.ኤ.አ. ለ2016 መጨረሻ የሚያስፈልገው የገንዘብ መጠን ክፍተት አሁንም እንዳለ መሆኑን የገለጸው ጽሕፈት ቤቱ በተለይ ለውኃ ወለድ ተቅማጥ በሽታ፣ ለእንስሳት ጤና ክብካቤ እገዛና ለምግብ ዕርዳታ አቅርቦት አስፈላጊው የገንዘብ መጠን ተሟልቶ እንዳልቀረበ አክሏል፡፡እ.ኤ.አ. በ2017 ለሚካሄደው የምግብ አቅርቦት፣ የጤና፣ የንፁህ የመጠጥ ውኃ አቅርቦት ከፍተኛ የገንዘብ ድጋፍ እንደሚያስፈልግ ተገልጿል፡፡ በህንድ ውቅያኖስ ላይ የታየው አሳሳቢ የአየር ፀባይ በአገሪቱ ምሥራቅና ደቡብ አካባቢዎች ድርቅ ያስከትላል የሚል ሥጋት አሳድሯል፡፡ በዚህም ሳቢያ የመኸር ምርት ሊቀንስ፣ የእንስሳት መኖና የውኃ እጥረት ሊከሰት እንደሚችል ጽሕፈት ቤቱና ሌሎች አጋር ድርጅቶች መተንበያቸው በመግለጫው ተካቷል፡፡ | 0 |
65d843700b06bc8af203e0229a648e95 | 85054221b8b2879660b532637df0a44d | በሶስት ከተሞች በ53 ነጥብ 7 ሚሊየን ዶላር ወጪ የተገነቡ የኃይል ማከፋፈያ ጣቢያዎች ተመረቁ | አዲስ አበባ፣ መጋቢት 9፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የካ ክፍለ ከተማ አስተዳደር በ3 ነጥ 2 ሚሊየን ብር ያስገነባቸውን 24 መኖሪያ ቤቶች አቅም ለሌላቸው ነዋሪዎች አስረከበ።የመኖሪያ ቤቶቹ በክፍለ ከተማው ወረዳ 13 መብራት ሐይል መጠለያ ተብሎ በሚጠራው ሰፈር የተገነቡ መሆኑ ተገልጿል።የክፍለ ከተማው ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ አስፋው ለገሰ የቤቶቹን ቁልፍ በዛሬው ዕለት ለባለእድለኞች አስረክበዋል።መኖሪያ ቤቱ ከተላለፈላቸው 24 ነዋሪዎች መካከል 6ቱ አካል ጉዳተኞች መሆናቸውን ከአዲስ አበባ ፕሬስ ሴክሬታሪያት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።በክፍለ ከተማው ወጪ በ6 ወራት ውስጥ ግንባታቸው የተጠናቀቀው እነዚህ ቤቶች እያንዳንዳቸው 24 ካሬ ሜትር ስፋት አላቸው ተብሏል።በክፍለ ከተማው የድሃ ድሃ ተብለው የተለዩ ከ15 ሺህ በላይ ቤት ፈላጊ ነዋሪዎች ይገኛሉ።ትኩስ መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት የቴሌግራም ገፃችንን ሰብስክራይብ ያድርጉ!
| 0 |
72d7bfbfd2a6cfa4b2d9fc85330518d0 | 72d7bfbfd2a6cfa4b2d9fc85330518d0 | ሪፖርት | ሀዋሳ ከተማ የዕለቱን ትልቅ ድል አስመዝግቧል | በኢትዮጵያ ፕሪምየር ሊግ ዛሬ ሀዋሳ ላይ ሀዋሳ ከተማ ወልዋሎ ዓዲግራት ዩኒቨርሲቲን አስተናግዶ ከፍፁም የጨዋታ ብልጫ ጋር 3-0 በመርታት የዓመቱን ጉዞ በድል ከፍቷል፡፡ የወልዋሎው አጥቂ ሪችሞንድ አዶንዶ ከቁምጣው ውስጥ ባደረገው የተለየ ትጥቅ እንዲሁም ለግብ ጠባቂው ዮሀንስ ሽኩር የህክምና ዕርዳታ በማስፈለጉ ጨዋታው ዘግየት ብሎ የጀመረ ነበር። በአማካዮቹ አዳነ ግርማ እና ታፈሰ ሰለሞን እንቅስቃሴ የሚመራው ሀዋሳ ከተማ በደስታ ዮሀንስ ድንቅ ብቃት ታግዞ በጨዋታው ፍፁም የሆነ ብልጫን ያሳየ ሲሆን ሪችሞንድ አዶንጎ ላይ የተመሰረተው የወልዋሎ የማጥቃት አማራጭ ስኬታማ መሆን ሳይችል ቀርቷል። 14ኛው ደቂቃ ላይ በጨዋታው ልዩነት ሲፈጥር የነበረው ደስታ ዮሀንስ በግራ የወልዋሎ የግብ መስመር እየገፋ ገብቶ ያደረገው ሙከራ የጨዋታው የመጀመሪያ ሙከራ ነበር። ደስታ 28ኛው ደቂቃ ላይ እስራኤል እሸቱ ላደረገው ሌላ ሙከራም ኳስ አመቻችቶ የሰጠ ሲሆን የሁለቱ ተጫዋቾች ጥምረት በዛው ቀጥሎ የወትሮው የመሀል ሜዳ የበላይነት ያልተለያቸው ሀዋሳዎችን 44ኛው ደቂቃ ላይ ቀዳሚ አድርጓል። ግቧን በግንባር በመግጨት ያስቆጠረው የፊት አጥቂው እስራኤል እሸቱ ሲሆን ከመስመር ኳስ ያሻገረለት ደግሞ ደስታ ዮሃንስ ነበር። የመጀመሪያው አጋማሽ የወልዋሎዎች ብቸኛ ሙከራ 31ኛው ደቂቃ ላይ ኦዶንጎ የተከላካዮችን ስህተት ተጠቅሞ በፈጠረው አጋጣሚ የተገኘ ሲሆን ሜንሳህ ሙከራውን ማዳን ችሏል። ቡድኑ ግብ ከተቆጠረበት በኋላ በጭማሪ ደቂቃ ምላሽ ለመስጠት በዋለልኝ ገብሬ ያደረገው ሙከራም ፍሬ ማፍራት አልቻለም።ቡድኑ ቀይሮ ወደ ሜዳ ያስገባቸው ወጣቶቹ አጥቂዎች ቸርነት አውሽ እና ብሩክ በየነ ተፅዕኖም ለሀዋሳ ተደጋጋሚ ሙከራዎችን መፍጠር ችሏል። 86ኛው ደቂቃ ላይ ከሁለቱ ተጫዋቾች ጥምረት ተገኝቶ ቸርነት የሞከረው እና ዮሃንስ ሽኩር ያወጣው ኳስ ለዚህ ማሳያ የሚሆን ነው። ነገር ግን ጭማሪ ደቂቃ ላይ ኮከብ ሆኖ ያመሸው ደስታ ዮሃንስ ከመሀል የላከውን ኳስ ታፈሰ ሰለሞን በአግባቡ ተቆጣጥሮ እና ሁለት የወልዋሎ ተከላካዮችን አልፎ ግብ ጠባቂው ዮሀንስ ሽኩርን አቅጣጫ በማሳት በድንቅ አጨራረስ ሶስተኛ ግብ ማስቆጠር ችሏል።
| 1 |
210f3f1c3f328b95ef2e6f2c2ed3235c | cdf6c712ed71da073246ea63c203d3fa | ከፍተኛ ሊግ | ደደቢት ተከላካይ አስፈረመ | በዝውውር መስኮቱ ከፍተኛ እንቅስቃሴ እያደረገ የሚገኘው እና በቅርቡ ወደ ዝግጅት የሚገባው መከላከያ የግራ መስመር ተከላካይ አስፈርሟል።ከሀዋሳ ከነማ የታዳጊ ቡድን አንስቶ እስከ ዋናው ቡድን ድረስ አምበል በመሆን ጭምር መጫወት የቻለው ደስታ ዮሐንስ ያለፉትን አራት ዓመታት በግራ መስመር ተከላካይነት ጥሩ ብቃት በማሳየት ጎልተው ከወጡ ተጫዋቾች መካከል አንዱ ነበር። ደስታ ከሀዋሳ ከተማ ውጪ በየትኛውም የፕሪምየር ሊግ ቡድን ያልተጫወተ ሲሆን ቀጣይ ክለቡን መከላከያ በማድረግ ለሁለት ዓመት የሚያቆየውን ፊርማውን አኑሯል።ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን መጫወት የቻለው ደስታ ባሳለፍነው ሁለት ዓመት በግራ የተከላካይ መስመር በኩል በሁነኛ ተጫዋች በማጣት ሲቸገሩ ለነበሩት መከላከያዎች ከአስናቀ ሞገስ ጋር በመሆን በቦታው ላይ የነበረውን ክፍተት ይቀርፋሉ ተብሎ ይገመታል።መከላከያዎች በዝውውሩ ሂደት እስካሁን ምንተስኖት አሎ፣ አስናቀ ሞገስ፣ ሐብታሙ ወልዴ፣ አንተነህ ተስፋዬ፣ ነስረዲን ኃይሉ፣ ፍቅረየሱስ ተ/ብርሃን፣ ሐብታሙ ገዛኸኝ እና ደስታ ዮሐንስን ማስፈረም ችለዋል። | 0 |
5d16b20c4a395ddb3c6714bb9e1205f6 | 4b7ce11ba6037463491838e48c62417e | እንግሊዝ ከመቅደላ የወሰደቻቸውን ቅርሶች ለማስመልስ መንግስት የተጠናከረ ጥረት እያደረገ ነው – ባህልና ቱሪዝም ሚኒስቴር | ባለፉት ዓመታት በምዕራብ ሐረርጌ ዞን በኦዳ ብልቱ አካባቢ ግንባታው የተከናወነው የባህል ማዕከል ሊመረቅ መሆኑን የኦሮሚያ ባህልና ቱሪዝም ቢሮ አስታወቀ ።የቢሮው የኮሚኒኬሽን ኃላፊ ወይዘሮ አሊፊያ ሃጂ ለዋልታ እንደገለጹት ከ20 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ሲገነባ የቆየው የባህል ማዕከል በክልሉ መንግሥትና በህዝቡ ድጋፍ የግንባታ ሥራው ተጠናቋል ።የባህል ማዕከሉ የኦሮሞን ባህል፣ ታሪክ ፣ ቅርሶች እንዲሁም የሐረርጌን የገዳ ሥርዓት ለማስተዋወቅ ትልቅ ጥቅም እንዳለው የጠቆሙት ወይዘሮ አሊፊያ የማዕከሉ ዲዛይን የአካባቢውን ሁኔታ እንዲያሳይ ተደርጎ የተሠራ መሆኑን ወይዘሮ አሊፊያ አስረድተዋል።የባህል ማዕከሉ በኦሮሚያ ክልል የባህል ሳምንት በሚከበርበት በመጪው መጋቢት 16 ዕለት ተመርቆ ለህብረተሰብ አገልግሎት ክፍት እንደሚሆን ወይዘሮ አሊፊያ አመልክተዋል ።የኦዳ ብልቱ ባህል ማዕከል በምዕራብ ሐረርጌ የሚገኘውን የገዳ ሥርዓትና ባህልን ይበልጥ ለማስተዋወቅ እንሚረዳ ይጠበቃል ። | 0 |
0f2780d793bfc9ec3cd29efecc42a640 | 547d27843aa0f6837f20002d4434fd90 | በኢትዮጵያ በኮሮና ቫይረስ የተያዘ 6ኛ ሰው ተገኘ | በኮሮና ቫይረስ በሽታ ምክንያት በሀገራችን በዛሬው እለት ሦስተኛው ሰው ህይወት ማለፉን ስገልጽ በከፍተኛ ሀዘን ነው። ታማሚዋ በለይቶ ማቆያ ከመጋቢት 28 ጀምሮ ህክምና ሲደረግላቸው የነበርና ከገቡበት ቀን ጀምሮ በጽኑ ህሙማን ክፍል ክትትል ላይ የነበሩ ናቸው። | 0 |
32d53f054b4575a29b9a12b305fc9e8f | ed9ff46ea453762c35eeaf07204ad21e | የ34 አመቷ ፊንላንዳዊት የአለማችን ወጣቷ ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነች | የመስመር አጥቂዋ መሳይ ተመስገን የመከላከያ ሁለተኛ ፈራሚ ሆናለች፡፡ከቀናት በፊት አሰልጣኝ በለጠ ገብረኪዳንን የመደቡት መከላከያዎች በአሰልጣኙ ሹመት ቀን ነፃነት ፀጋዬን ከአዳማ ከተማ ማስፈረማቸው የሚታወሶ ሲሆን በዛሬው ዕለት ደግሞ ወጣቷ የመስመር አጥቂ መሳይ ተመስገንን በሁለት ዓመት ኮንትራት አስፈርመዋል፡፡ ከኢትዮጵያ ወጣቶች ስፖርት አካዳሚ የተገኘችውና በኢትዮ ኤሌክትሪክ ሁለት ተስፋ ሰጪ የውድድር ዓመታት ያሳለፈችው ተጫዋቿ ከአዳማ ከተማ ጋር ቅድመ ስምምነት ብትፈፅም ለመከላከያ ለመጫወት ዛሬ በይፋ ፈርማለች፡፡ | 0 |
488a20d7fda96108c55798a4a114c306 | 8ca12d1ee6b28b8fa742fdd15bfb8147 | የአለም የጤና ተቋማት በኮቪድ 19 መዛመት ምክንያት መራቆታቸው ተገለጸ | አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኮቪድ-19 ወረርሽኝ ምክንያት ለችግር ለተጋለጡ በውጭ አገር ለሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን ዜጎች ድጋፍ በሚደረግበት ዙሪያ በኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር መሰብሰቢያ አዳራሽ ከባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ ሰኔ 5 ቀን 2012 ዓም ውይይት ተደርጓል።ውይይቱን በኢፌዲሪ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ደኤታ ወ/ሮ ጽዮን ተክሉ የተመራ ሲሆን፤ በውይይቱ የሰላም ሚኒስትር ደኤታ ፍሬአለም ሽባባው፣ የሰራተኛና ማህበራዊ ጉዳይ ሚኒስትር ደኤታ ወ/ሮ አየለች እሸቴ፣ የአውሮፓ ህብረት አምባሳደር ጆሃን ቦርግስታም፣ የተ.መ.ድ ኤጀንሲዎች በኢትዮጵያ አስተባባሪ ዶ/ር ካትሪን ሶዚ እና የአለም አቀፍ ስደተኞች ድርጅት የኢትዮጵያበተ.መ.ድ በወጣው መግለጫ እና በአፍሪካ ህብረት ኮሚኒኬ መሰረት የሰዎች እንቅስቅቃሴ በአሁኑ ስዓት ያለውን የኮሮና ወረርሽኝ ተጋላጭነትን እንደሚጨምር ሁሉም አካላት ግንዛቤ መያዝ እንደሚያስፈልግ በውይይቱ ተነስቷል።ከዚህም በተጨማሪ በኢትዮጵያ የኮቪድ-19 ስርጭት ከቀን ወደ ቀን በከፍተኛ ሁኔታ እየጨመረ የመጣ በመሆኑ ዜጎች ባሉበት አገር አስፈላጊው ድጋፍ እየተደረገላቸው እንዲቆዩ ማድረግ የተሻለ አማራጭ እንደሚሆን ግንዛቤ ተይዟል።ለዚህም የሚመለከታቸው ዓለም አቀፍ እርዳታ ሰጪ ድርጅቶች አስፈላጊውን ድጋፍ እንዲያደርጉ እና ኢትዮጵያም አለም አቀፉን ወረርሽኙን በመቆጣጠር ረገድ ተሳትፎዋ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተገልጿል። | 0 |
272e891cfebe20a3a4a2d6571e044f8c | dd580e79dbf45fad21217a81304c5255 | ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ከመንግሥታቱ ድርጅት ምክትል ዋና ጸሃፊ ጋር በጁሃንስበርግ መከሩ | በጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማሪያም ደሳለኝ የሚመራ ከፍተኛ ልዑክ ቻይና ከጃፓን ቅኝ አገዛዝ ነጻ የወጣችበትንና የሁለተኛውን የዓለም ጦርነት ፍጻሜ ለመዘከር ባዘጋጀችው ፕሮግራም ላይ ለመታደም ዛሬ ወደ ቤጂንግ አመራ።ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናትና የንግዱን ማህበረሰብ አባላት የያዘው ልዑክ በቆይታው ከቻይና ባለሃብቶች ጋር እንደሚመክርና የሁለትዮሽ ውይይቶችም እንደሚያካሂድ ይጠበቃል።የቻይና መንግሥት እንደ አውሮፓዊያን አቆጣጠር መስከረም 3 ቀን የአገሪቱ ብሔራዊ ቀን ሆኖ እንዲከበር ባሳለፈው ውሳኔ መሠረት አገሪቱ ለመጀመሪያ ጊዜ ይህን የነጻነት ቀኗን ከነሐሴ 28 እስከ ነሐሴ 30 ቀን 2007 ዓ.ም በተለያዩ መርሃ ግብሮች ታከብራለች።“ቻይና የጃፓንን ወረራ ለመከላከል ያደረገችው ጦርነትና የዓለም ጸረ ፋሽስት ጦርነት ድል መታሰቢያ ቀን 70ኛ ዓመት” የበዓሉ ይፋዊ መጠሪያ ሆኗል።እንደ አውሮጳውያን አቆጣጠር በ1945 ነበር የሁለተኛው የዓለም ጦርነት ፍጻሜውን ያገኘው ቻይናም እንዲሁ ነጻ አገር የሆነችው።ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለማርያም ደሳለኝን ጨምሮ የተለያዩ አገራት ርዕሳነ መንግሥታት በበዓሉ ላይ እንዲታደሙ ጥሪ ቀርቦላቸዋል።በዚሁ መሠረትም የሩሲያው ፕሬዚዳንት ቭላድሚር ፑቲንና የደቡብ አፍሪካው ጃኮብ ዙማን ጨምሮ የ30 አገራት መሪዎች በበዓሉ ላይ እንደሚታደሙ ይጠበቃል።ከ19 አገራት የተውጣጡ የመንግስት ተወካዮችና የተባበሩት መንግስታት ዋና ጸሃፊ ባንኪ ሙንን ጨምሮ 10 የዓለም ዓቀፍ ተቋማት ኃላፊዎች በበዓሉ ላይ እንደሚታደሙ የቻይና መንግስት አስታውቋል።የቀድሞው የእንግሊዝ ጠቅላይ ሚኒስትር ቶኒ ብሌየርና የጀርመን መራሄ መንግሥት የነበሩት ጌራርድ ሽሩደርን ያካተተ ስድስት የቀድሞ ፖለቲከኞችም የበዓሉ ታዳሚ ለመሆን ማረጋገጫ ሰጥተዋል።በዓሉንም ለመዘገብ ከአገር ውስጥና ከተለያዩ አገራት የተውጣጡ 3 ሺህ 500 ጋዜጠኞችም የፕሮግራሙ ታዳሚዎች እንደሚሆኑ ይጠበቃል።በበዓሉ በዓይነቱ ለየት ያለ ግዙፍ ወታደራዊ ትርዒት እንደሚኖር የቻይና መንግሥት መግለጫ ያመለከተ ሲሆን የሩሲያ ወታደሮችን ጨምሮ የተለያዩ አገራት ሠራዊቶች የወታደራዊ ትርኢቱ ተሳታፊ እንደሚሆኑ ይጠበቃል።ባለፈው ዓመት ቻይና በዓሉን ለመጀመሪያ ጊዜ ስታከብር ጂን ፒንግ፣ ሰባት የፖሊት ቢሮ ቋሚ ኮሚቴ አባላት፣ ዘማቾች፣ ተማሪዎችና የጦር ኃይሉ ከጃፓን ጋር የተካሄደውን ጦርነት ለማሰብ ከተቋቋመው ሙዚየም ፊት ለፊት በሚገኘው የሉጎው ድልድይ በዓሉን ታድመው ነበር። | 0 |
0eda1924b81cc83b0b1931c296858e89 | 179a76303e189c0758ba4dd41c936028 | “እግዚያብሔር ይህንን ነገር ያደረገው የኢትዮጵያን ሕዝብ ሊያስተርም ነው ብዬ አስባለሁ”- በአይሮፕላን አደጋው ልጃቸውን ያጡ እናት | በቅዱስ ጊዮርጊስ ሦስት ዓመት ቆይታ ያደረገው እና በቅርቡ ወደ ወልቂጤ ከተማ ለመመምራት የተስማማው አሜ መሐመድ ስላለው ወቅታዊ ሁኔታ ይናገራል።በጅማ አባ ቡና ቀሪ አንድ ዓመት ኮንትራት ቢኖረውም የውል ማፍረሻ አንድ ሚሊዮን ብር በመክፈል በ2010 ወደ ፈረሰኞቹ ቤት ማምራቱ ይታወቃል። በቅዱስ ጊዮርጊስ ሦስቱን ዓመት ካገለገለ በኃላ በቅርቡ ወደ ወልቂጤ ማምራቱ ይታወቃል። ይህን ተከትሎ ሶከር ኢትዮጵያ አሜ መሐመድን አግኝታ በቅዱስ ጊዮርጊስ ስለነበረው ቆይታ እና ስለለቀበት ምክንያት እንዲሁም ከአዲሱ ክለቡ ወልቂጤ ከተማ ጋር ስለሚያስበው ቆይታ ይሄን ነግሮናል።” በቅዱስ ጊዮርጊስ እኔ በግሌ ጥሩ ጊዜ አሳልፌለው ብዬ አስባለሁ፤ ያው አንዳንድ ነገሮች ቢኖሩም በቅዱስጊዮርጊስ ደስተኛ ሆኜ ነበርኩ። ቀሪ የአንድ ዓመት ኮንትራት የነበረኝ ቢሆንም ክለቡ አዳዲስ ተጫዋች በማምጣቱ ከአመራሮች ጋር ተነጋግሬ በውሰት ወደ ወልቂጤ ከተማ አምርቻለው። ወደ ወልቂጤ ያመራሁት በቂ የመጫወት እድል እንደማገኝ በማመን ነው። ራሴንም በሁሉም መንገድ አዘጋጅቼ በወልቂጤ የተሳካ ዓመት አሳልፋለው ብዬ ተስፋ አደርጋለሁ።” ብሏል።ፈጣኑ አጥቂ አሜ መሐመድ ከቅዱስ ጊዮርጊስ በተጨማሪ ከዚህ ቀደም በመከላከያ ተስፋ ቡድን የእግርኳስ ጅማሬውን በማድረግ በጅማ አባ ቡና የተሳካ የውድድር ዓመት በማሳለፍ በኢትዮጵያ ከ20 ዓመት በታች እና በዋናው ብሔራዊ ቡድን መጫወቱ ይታወቃል። | 0 |
4398750270a69e65f945204f4b29f568 | 7cf10074dda446cd8e871a427f409a1f | ርእሰ መሥተዳድሩ በሰሜን ሸዋ ዞን የምንጃር ሸንኮራ ወረዳ የመስኖ ልማት እንቅስቃሴን ጎበኙ፡፡ | አዲስ አበባ፣ ነሃሴ 20፣ 2012(ኤፍ ቢ ሲ) በሰሜን ሸዋ ዞን እንሳሮ ወረዳ የጣለ ከባድ ዝናብን ተከትሎ በተከሰተ ጎርፍ የሶስት ታዳጊወች ህይወት አለፈ።የሰሜን ሸዋ ዞን ፖሊስ መምሪያ የኮሙዩኒኬሽንና ሚዲያ ዋና ክፍል ኃላፊ ኮማንደር ተስፋዬ ግዛቸው በእንሳሮ ወረዳ ላም ገኖ ቀበሌና አካባቢው የጣለውን ከባድ ዝናብ ተከትሎ በስፍራው የነበሩ የአንድ ቤተሰብ አባላት የሆኑ የ19፣16 እና 11 ዓመት ሁለት ወንድና አንድ ሴት ወደ ቤታቸው ሲመለሱ ሰጠኝ በተባለ ወንዝ በመወሰዳቸው ህይወታቸው ማለፉን ተናግረዋል።በአካባቢው ነዋሪዎች በተደረገ ፍለጋ የሶስቱም እህትና ወንድማማቾች አስከሬን መገኘቱንም ነው የተናገሩት፡፡ኮማንደር ተስፋዬ አያይዘውም በክረምት ወቅት ከሚከሰቱ አደጋዎች ህብረተሰቡ ጥንቃቄ እንዲያደርግም ጥሪ አቅርበዋል፡፡በግርማ ነሲቡ | 0 |
ea6b4202b49c08387635f71beaad0d02 | 760aa156fe392141694d26eec738d2ef | 170 መንገደኞችን አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ ቦይንግ 737 አውሮፕላን ኢራን ውስጥ ተከሰከሰ | አዲስ
አበባ፡- ከአዲስ አበባ ወደ ናይሮቢ ሲጓዝ ቢሾፍቱ አካባቢ የተከሰከሰው የቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላን አብራሪዎች በአምራቹ ቦይንግም ይሁን በአሜሪካ የፌዴራል አቪዬሽን ባለሥልጣን የተቀመጡ መስፈርቶችን ያሟሉ እንደነበሩ የምርመራው የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት ማመላከቱ ተገለፀ፡፡ የትራንስፖርት
ሚኒስትሯ ወይዘሮ ዳግማዊት ሞገስ እንደገለጹት፤ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ንብረት የሆነው ቦይንግ 737 ማክስ 8 አውሮፕላን አደጋ የምርመራ ሂደት ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን አደጋ የምርመራ ሂደትና አሰራርን ተከትሎ የተከናወነ መሆኑን ተናግረዋል፡፡ የምርመራ ሂደቱን አደጋው የደረሰበት አገር በቀዳሚነት እየመራ የአውሮፕላኑ አምራች አገር፣ የአውሮፕላኑን ንድፍ (ዲዛይን) የሠራው አገር እና እንደ አስፈላጊነቱ ሌሎች አካላትም በዓለም አቀፍ ሕጉ መሰረት ተሳትፈውበታል ያሉት ሚኒስትሯ ምርመራው ያለምንም ችግር መካሄዱን ገልጸዋል፡፡ የመርማሪ
ቡድኑ በአውሮፕላኑ አደጋ የመጀመሪያ ደረጃ ሪፖርት ተመስርቶ ያስቀመጣቸው እውነታዎችና ምክረ ሐሳቦች፤ አውሮፕላኑ መብረር የሚያስችል ሰርተፍኬት ያለው መሆኑ፣ አብራሪዎቹ ይሄንን በረራ ማድረግ የሚያስችላቸው ተገቢው የምርመራ ብቃት ያላቸው መሆኑ፣ አውሮፕላኑ ለበረራ ሲነሳ በትክክለኛው መስመር ለመብረር በሚያስችለው ሁኔታ ላይ መሆኑ እና አብራሪዎቹ አውሮፕላኑን ለመቆጣጠር ያስችላል ተብሎ በአምራቹ ቅደም ተከተል መሰረት ማከናወን መቻሉን መርማሪ ቡድኑ ማረጋገጡን ሚኒስትሯ ተናግረዋል፡፡ የመርማሪ ቡድኑ መሪዎችና አባሎች አውሮፕላኑ በሰላም ተንደርድሮ የተነሳ እንደነበር ማወቃቸውን የገለጹት ሚኒስትሯ፤ በረራው ከተጀመረ በኋላ በተደጋጋሚ የአውሮፕላኑ አፍንጫ መደፈቅ ሲያሳይ አብራሪዎቹ አውሮፕላኑን ለመቆጣጠር ያስችላል ተብሎ በአምራቹ የተሰጠውን የበረራ ቅደም ተከተል ተከትለው አውሮፕላኑን በተደጋጋሚ ለመቆጣጠር ቢሞክሩም እንዳልቻሉ ተገልጿል፡፡ በተጨማሪም ከአውሮፕላኑ የመረጃ ሳጥን የተገኘው መረጃ ከውጭ አካል በአውሮፕላኑ ላይ የደረሰበት ጥቃት እንደሌለም ጠቁሟል፡፡ የአደጋው ሙሉ ሪፖርት በዓመት ውስጥ ተጠናቅቆ እንደሚወጣም ተጠቁሟል፡፡አዲስ ዘመን መጋቢት 27/2011ሙሐመድ
ሁሴን | 0 |
1cf0efe922a61800c416b5f8abf7ad03 | f4d5c024234e86a2941922f398361111 | በአዲስ አበባ የማበረሰብ ጤና መድህን ስራን ተደራሽ ለማድረግ እየሰራ መሆኑን ቢሮው አስታወቀ | አዲስ አበባ ፣ ሰኔ 8 ፣ 2012 (ኤፍ ቢ ሲ) በአዲስ አበባ በኮሮና ቫይረስ የተያዙ ሰዎች ቁጥር 2 ሺህ 577 መድረሱን የአዲስ አበባ ከተማ ጤና ቢሮ አስታወቀ።ቢሮው በፌስ ቡክ ገጹ ባወጣው መረጃ ባለፉት 24 ሰዓታት በተደረገ የላቦራቶሪ ምርመራ 98 ሰዎች ቫይረሱ እንደተገኘባቸው ገልጿል።ከኮሮና ቫይረስ ጋር በተገናኘም በህክምና ማዕከል ውስጥ ህክምና ሲከታተል የነበረ የ19 አመት ወጣት ህይወቱ ማለፉንም አስታውቋል።በሌላ በኩል ደግሞ በትናንትናው እለት 31 ሰዎች ከአዲስ አበባ ከኮሮና ቫይረስ አገግመዋል ነው ያለው። | 0 |
b141f85103fb75e52e9986be0a3b025f | b141f85103fb75e52e9986be0a3b025f | በኢትዮጵያ የሚታዩ የሚዲያ ልማት መስፋፋቶች በቂ አይደሉም – መንግስት | የፕሬስ ነፃነት ቀን ዛሬ በዓለም ለ26ኛ በኢትዮጵያ ደግሞ ለ8ኛ ጊዜ ዛሬ በጽሕፈት ቤቱ አዳራሽ ተከብሯል ፡፡በበዓሉ የተገኙት ሚኒስትሩ ዶክተር ነገሪ ሌንጮ እንደገለጹት፤በመንግስትና በግሉ ዘርፍ ያሉት የሚዲያ ልማቶች ከህብረተሰቡ ፍላጎት አኳያ በቂ አይደሉም ፡፡ይህም መንግስት የግልም ይሁን የራሱን ሚዲያዎች አለማበረታታት፣ የመገናኛ ብዙሃን መሳሪያዎች ቀረጥ መናር እና በሚዲያ አገልግሎት የተገኘ ትርፍ 40 ከመቶ ለመንግስት የሚከፈል መሆኑ ዋንኛ ማነቆዎች መሆናቸው ነው የተመለከተው ᎓᎓እነዚህን ችግሮች በማጥናት ለመንግስት የሚያቀርብ ኮሚቴ በቅርቡ ተቋቁሞ ወደ ስራ እንደሚገባ በውይይቱ ተጠቁሟል ᎓᎓በዚሁ በዓል የኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን በእውቀት፣ በክህሎትና በሙያ ብቃት ማነስ ሳቢያ የህብረተሰቡ ችግሮች ነቅሰው ለማውጣት ብቃት ማጣታቸውን ነው ሚኒስትሩ ያስገነዘቡት ።የአገሪቱ ሚዲያዎች በተጨባጭ መረጃዎች ላይ ተመስርቶ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በማጋለጥ የህግ የበላይነት እንዲከበር ከማድረግ አንጻርም ከፍተኛ እጥረት እንዳባቸውም ገልጸዋል ።ብቃት ባላቸውና ሙያዊ ስነ-ምግባር በተላበሱ ጋዜጠኞች የተደራጁ የሚዲያ ተቋማት እንዲፈጠሩ መንግስት የበኩሉን ጥረት ማድረግ እንደሚጠበቅበት ነው ያስረዱት ።በበዓሉ ጥናታዊ ጽሑፍ ያቀረቡት የሪፖርተር ጋዜጣ ባለቤት አቶ አማረ አረጋዊ በበኩላቸው የግልም ሆኑ የመንግስት ሚዲያ ተቋማት ከራሳቸው የሚመነጩ ድክመቶች እንዳሉባቸው ጠቁመው በተለይ በመንግስት በኩል ድጋፍ ስለማይደረግላቸው ደካማ መሆናቸውን አስገንዝበዋል ።"በተለይ የግሉ ዘርፍ የሚዲያ ህጎችና የፕሬስ ነጻነትን ተግባራዊ የማድረግ ክፍተቶች አሉበት" ብለዋል ። ስለሆነም መንግስት የመገናኛ ብዙሀንን መደገፍ እንዳለበት አቶ አማረ አሳስበዋል ፡፡ | 1 |
8da98abdd9075cd53b8549f6964ce6d7 | 8da98abdd9075cd53b8549f6964ce6d7 | የአንዳርጋቸው ፅጌ እህት ብዙአየሁ ፉሮ ከኢትዮጵያ ተባረሩ | የመን ለኢትዮጵያ መንግሥት አሣልፋ የሰጠቻቸው የግንቦት ሰባት የፍትሕ፣ የነፃነትና የዴሞክራሲ ንቅናቄ ዋና ፀሐፊ አቶ የአንዳርጋቸው ፅጌ እህት ወ/ሮ ብዙአየሁ ፉሮ ከኢትዮጵያ በአንድ ቀን ውስጥ እንዲወጡ መደረጉት ለቪኦኤ ገልፀዋል፡፡ወ/ሮ ብዙአየሁ የወንድማቸውን የአቶ አንዳርጋቸውን ጉዳይ በቅርብ ለመከታተል ወደ ኢትዮጵያ ሄደው ለአሥር ቀናት ከቆዩ በኋላ ወደ ኢሚግሬሽን መሥሪያ ቤት ተጠርተው ወዲያው ሃገር ለቅቀው እንዲወጡ መታዘዛቸውን ተናግረዋል፡፡ኢትዮጵያ ውስጥ በቆዩባቸው ቀናት ውስጥ ወንድማቸው የሚገኙበትን ለማወቅ እንዲረዷቸው ወደ እንግሊዝ ኤምባሲና ወደ ዓለምአቀፍ ቀይ መስቀል ኮሚቴ መሄዳቸን፣ እንዲሁም ምናልባት አቶ አንዳርጋቸው ፍርድ ቤት ቢቀርቡ በሚል አዲስ አበባ የሚገኘው የእንግሊዝ ኤምባሲ ባሳሰባቸው መሠረት ጠበቃ ለመቅጠር ወዲያ ወዲህ ይሉ እንደነበር አመልክተዋል፡፡እዚያ በቆዩባቸው ቀናት ውስጥ ስለኢትዮጵያ መንግሥትም ይሁን ስለሌላ ማንምና ስለምንም ሁኔታ የነቀፌታም ይሁን የድጋፍ ቃል አለመናገራቸውን፣ ያደረጉት አንዳችም የሚያስባርር አድራጎት እንደሌለም ገልፀዋል፡፡ለዝርዝሩ ወ/ሮ ብዙአየሁ ፉሮ ከቪኦኤ ጋር ያደረጉትን አጭር ቃለምልልስ ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያዳምጡ፡፡ | 1 |
65533c63c10c69db8d851247c7629cc0 | 65533c63c10c69db8d851247c7629cc0 | በኢትዮጵያ የኮሮናቫይረስ መመርመሪያ ኪት ሊመረት ነው | አዲስ አበባ፣ ጳጉሜን 1፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኢትዮጵያ የኮሮናቫይረስ መመርመሪያ ኪት ከአንድ ወር በኋላ ማምረት እንደሚጀመር የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ።የጤና ሚኒስቴር ሚኒስትር ዴኤታ ዶክተር ደረጀ ዱጉማ እንደተናገሩት ኮሮናቫይረስን የመመርመር አቅምን ከፍ ለማድረግ በርካታ ሥራዎች እየተሰሩ ነው።በአሁኑ ወቅትም ከአንድ ወር በኋላ ከቻይና መንግሥት ጋር በመተባበር የመመርመሪያ ኪት ለማምረት ቅድመ ዝግጅት እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።ለእዚህም ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር ዐቢይ አህመድ ድጋፉን ከምታደርገው የቻይና መንግሥት ጋር በጉዳዩ ላይ እየመከሩ መሆኑን ገልጸዋል።የመመርመሪያ ኪቱን በአገር ውስጥ ማምረት ሲጀመር ከውጭ የሚገባውን ኪት ሙሉ በሙሉ ያስቀራል ያሉት ዶክተር ደረጀ ምርቱ ለሌሎች የአፍሪካ አገራት እንደሚዳረስም ተናግረዋል።በሌላ በኩል በአሁኑ ወቅት የኢንፌክሽን መከላከያ ግብዓቶች በኢትዮጵያ በስፋት መመረት መጀመራቸውን ጠቁመው፣ የኮሮናቫይረስ መከላከያ ቁሶችን ወደ ውጭ አገራት መላክ መጀመሩንም ገልጸዋል።በሐዋሳ ኢንዱስትሪያል ፓርክ እነዚህን ቁሶች የሚያመርቱ ኩባንያዎች ቀዳሚ መሆናቸውን ሚኒስትር ዴኤታው መናገራቻን ኢዜአ ዘግቧል፡፡በኢትዮጵያ በአሁኑ ወቅት 52 የኮሮናቫይረስ መመርመሪያ ማዕከላት የሚገኙ ሲሆን በእነዚህም በቀን ከ20 ሺህ በላይ ናሙናዎችን መመርመር ተችሏል። | 1 |
b8be683557df519fd7d03748cb0c3034 | d92c03aa754f193c505ad7d439f1da42 | ኢትዮጵያ ውስጥ የላቀ ጣዕም ያለውን የቡና ዓይነት የሚለይ ውድድር ተካሄደ | አዲስ አበባ፣ ጥር 2፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የሀላባን የዘመን መለወጫ በዓል ምክንያት በማድረግ የ8 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር በሀላባ ቁሊቶ ከተማ ተካሄደ።“ሴራችን ለሰላማችን” በሚል ሀሳብ በተካሄደው የሩጫ ውድድር ላይ የአካባቢው ነዋሪዎች ተሳትፈዋል።ውድድሩን ያስጀመረችው አትሌት ፋንቱ ምጌሶ “ሰላም ለሁሉም ነገር መሠረት በመሆኑ የሀላባ ብሄር የዘመን መለወጫ በዓሉን ከሰላም ጋር በማስተሳሰር መከበሩ ልዩ ያደርገዋል” ብላለች።በውድድሩ ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ለወጡ የገንዘብና የተሳትፎ የምስክር ወረቀት ሽልማት እንደተበረከተላቸው ከኢዜአ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ የሀላባ ብሄር ዘመን መለወጫ በዓል ዛሬና ነገ በተለያዩ ዝግጅቶች ይከበራል። | 0 |
77f14d56e7722f7aed4f3bce0ed0e4f6 | 522d72c2df6ca732001d0c73f3a2f094 | ሕወሓት የኢሕአዴግ አባል ድርጅቶች ካፈሩት ሀብት ድርሻዬን በሕግ እጠይቃለሁ አለ | አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 25 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአማራ ብሔራዊ ንቅናቄ (አብን) እና የኢትዮጵያ ዜጎች ለማኅበራዊ ፍትህ(ኢዜማ) ሕወሓት በትግራይ ክልል በሚገኘው የኢፌዴሪ መከላለከያ ሠራዊት ላይ የከፈተውን ጥቃት እንደሚያወግዙ አስታወቁ፡፡ፓርቲዎቹ ዛሬ ባወጡት መግለጫ እንዳስታወቁት መንግሥት በሕወሓት ላይ የሚወስደውን ሕግ የማስከበር ሥራ ይደግፋሉ፡፡ሕወሓት በትግራይ ክልል በሚገኘው የአገር መከላከያ ካምፕ ላይ እና በአማራ ክልል ዳንሻ እና ሶሮቃ በኩል ጥቃት ማድረሱን ተከትሎ መንግሥት እየወሰደ ያለው የሕግ ማስከበር ሥራ ፍፃሜ እንዲያገኝ ሕዝብን ማስተባበር ያስፈልጋል ብሏል።ሕዝቡ በመንግሥት የሚሰጡ የጥንቃቄ መልዕክቶችን በመቀበል ራሳቸውን እና አካባቢያቸውን እንዲጠብቁ አብን አሳስቧል።በሌላ በኩል ሕወሓት በተለያዩ ጊዜያት ሲያስተላልፋቸው የነበሩ የሥርዓት አልበኝነት ጥሪዎች እና በክልሉ ሕግን ተላልፎ ሲፈጽም የነበራቸው ድርጊቶች አልበቃ ብለውት የኢትዮጵያ ሉዓላዊነት ምልክት በሆነው መከላከያ ሠራዊት ላይ የፈፀመው ጥቃት በፍፁም በዝምታ የሚታለፍ እንዳልሆነ እናምናለን ብሏል ኢዜማ በመግለጫው።የነበረው ችግር በንግግር መፈታት ከሚችልበት ምዕራፍ አልፎ አሁን የደረሰበት ደረጃ መድረሱ በጣም አሳዝኖናልም ብሏል።ፓርቲዎቹ በሚወሰዱ እርምጃዎች ሰላማዊ ዜጎች ምንም ዓይነት ጉዳት እንዳይደርስባቸው አስፈላጊው ጥንቃቄ መደረግ እንደሚገባውም አስታውሰዋል። | 0 |
20b9127a70ebca94bfce1f4ab9b64873 | 7218c8c1208ac0c6ee7c1c83c0c417c3 | የኢትዮጵያ ህዝብ ብዛት 85 ነጥብ 9 ሚሊየን ደረሰ | አዲስ አበባ፡- በኢትዮጵያ በትላትናው ዕለት 85 ሰዎች ከኮሮና ቫይረስ ማገገማቸውን ተከትሎ ከቫይረሱ ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 934 መድረሱን የጤና ሚኒስቴር አስታወቀ፡፡
የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር ሊያ ታደሰ በዕለታዊ የኮሮና ቫይረስ ሪፖርታቸው ላይ እንደገለጹት በትላንትናው ዕለት በ24 ሰዓት ውስጥ በተደረገው 4 ሺህ 853 የላብራቶሪ ምርመራ 195 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው ጠቁመዋል፡፡
በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 3 ሺህ 954 መድረሱንም የጤና ሚኒስትሯ አስታውቀዋል።
ከዚህም ባለፈ በህክምና ማዕከል ውስጥ በህክምና ላይ የነበሩ ሁለት ሰዎች ህይወት ማለፉን ሚኒስትሯ አስታውቀዋል፡፡ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ የተገኘባቸው እና ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር 65 ደርሷል።
በሌላ መልኩ በትላንትናው ዕለት ካገገሙት 85 ሰዎች ውስጥ 73 ከአዲስ አበባ፣ 5 ከኦሮሚያ ክልል፣ 5 ከአማራ ክልል እና 2 ከትግራይ ክልል መሆናቸውን ሚኒስትሯ አስታውቀዋል።
አዲስ ዘመን ሰኔ 12/2012 | 0 |
4f0f6692906a6a19535502fe444dbd08 | 4f0f6692906a6a19535502fe444dbd08 | በግማሽ የበጀት ዓመቱ 2 ነጥብ 5 ሚሊየን ሊትር ኢታኖል ከቤንዚል ጋር በማደባለቅ አገልግሎት ላይ መዋሉ ተገለፀ | በግማሽ የበጀት ዓመቱ 2 ነጥብ 5 ሚሊየን ሊትር ኢታኖልን ከቤንዚል ጋር በማደባለቅ 2 ነጥብ 3 ሚሊየን ዶላር ማዳን መቻሉን የውሃ መስኖና ኢነርጂ ሚኒስቴር አስታወቀ።በሚኒስቴሩ የሕዝብ ግንኙነትና የኮሙኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ ብዙነህ ቶልቻ ለዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል እንደገለፁት፤ ባለፉት ስድስት ወራት የተመረተው 2 ነጥብ 5 ሚሊየን ሊትር ኢታኖል በነባር የስኳር ፋብሪካ በሆኑት በፊንጫና በመተሃራ ስኳር ፋብሪካዎች ነው። የባዮ ኢታኖል ምርት በሁለት ነባር ስኳር ፋብሪካዎች የሚመረት መሆኑን የገለፁት አቶ ብዙነህ፤ የፊንጫ ስኳር ፋብሪካ በዓመት እስከ 20 ሚሊየን ሊትር የሚያመርት ሲሆን፤ የመተሃራ 12 ነጥብ 5 ሚሊየን ሊትር ኢታኖል የማምረት አቅም ይኖራል ብለዋል።በአጠቃላይ በአምስት ዓመቱ የእድገትና ትራንስፎርሜሽን እቅድ መሰረት ከ10 ያላነሱ አዳዲስ የስኳር ፋብሪካዎች በተለያዩ የሀገሪቱ ክልሎች እንደሚገነቡ ጠቁመው፤ በ2007 ዓ.ም እስከ 181 ሚሊየን ሊትር ኢታኖል ማምረት እንደሚቻልና 64 ነጥብ 4 ሚሊየን ሊትሩን ከቤንዚል ጋር በማደባለቅ በአሁኑ ገበያ ዋጋ እስከ 57 ሚሊየን ዶላር የውጭ ምንዛሬ ማዳን ይቻላል ተብሎ እንደሚገመት ተናግረዋል።እንዲሁም 25 በመቶ ኢታኖልን ከ75 በመቶ ቤንዚል ጋር ማደባለቅ የሚቻልበት ደረጃ ላይ ይደረሳል ተብሎ እንደሚጠበቅ አቶ ብዙነህ ገልፀዋል። እስካሁን ባለው ሁኔታ ከ5 በመቶ እስከ 10 በመቶ ኢታኖል የማደባለቅ ስራ እየተከናወነ መሆኑን ገልፀው፤ ከ10 በመቶ በላይ ለማድረስ ግን መኪናዎችን የማሻሻል እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል።በመሆኑም ይህን ተግባራዊ ለማድረግ ከትራንስፖርት ሚኒስቴር ጋር በመተባበር ጥናት በመካሄድ ላይ ይገኛል ብለዋል።ኢታኖልን ከቤንዚል ጋር የማደባለቁ ስራ ጥቅምት 2001 ዓ.ም መጀመሩን የገለፁት አቶ ብዙነህ የማደባለቁ ስራ ከጀመረበት ጊዜ ጀምሮ እስከ አሁን 41 ነጥብ 77 ሊትር ኢታኖል ከቤንዚል ጋር ማደባለቅ መቻሉን ተናግረዋል።በዚህም ከ33 ነጥብ 23 ሚሊየን ዶላር በላይ ለቤንዚል ይውል የነበረ የውጭ ምንዛሬን ማዳን እንደተቻለ ዋልታ ኢንፎርሜሽን ማዕከል ዘግባ ያስረዳል። | 1 |
36ad6392c9a511c011f9578ada2d07a9 | 6ef06fff630b13bceac0b79d3e3a9597 | በመዲናዋ 150 በጎ ፍቃደኛ የትራፊክ አስተባባሪዎች ተመረቁ | አዲስ አበባ፣ ሰኔ 11፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) በኦሮሚያ ክልል በሰበታ እና ጅማ ከተሞች ግንባታቸው የተጠናቀቁ የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች ተመረቁ። የኦሮሚያ ብሄራዊ ክልላዊ መንግስት ቀጣይነት ያለውን ልማት በማስቀደም እና ለክልሉ ነዋሪዎች ተጠቃሚነት ልዩ ትኩረት በመስጠት 3 ሺህ 981 ግንባታቸው ለረጅም ጊዜ የተጓተቱ እና አዳዲስ የልማት ፕሮጀክቶችን 4 ነጥብ 81 ቢሊየን ብር በጀት መድቦ በማጠናቀቅ እያስመረቀ እንደሚገኝ የክልሉ የመንግስት ኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ቢሮ መረጃ ያመለክታል። በዛሬው እለትም በሰበታ ከተማ በ563 ሚሊየን ብር በሆነ ወጪ የተገነቡ 76 የተለያዩ የማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ የልማት ፕሮጀክቶች ተመርቀዋል። ግንባታቸው የተጠናቀቁ የልማት ፕሮጀክቶቹን በምክትል ርእሰ መስተዳድር ማዕረግ የማህበራዊ ዘርፍ አስተባባሪ አቶ አዲሱ አረጋን ጨምሮ ከፍተኛ የክልሉ የመንግስት የስራ ሀላፊዎች በተገኙበት ተመርቀዋል። ከተመረቁ ፕሮጀክቶች መካከልም የመማሪያ ክፍሎች፣ 23 ኪሎ ሜትር የውስጥ ለውስጥ ጌጠኛ ድንጋይ (ኮብል ስቶን) መንገዶች፣ የከተማ ፓርክ እና የመጠጥ ውሃ ፕሮጀክቶች ይገኙበታል። በተመሳሳይ በጅማ ከተማም ከ2010 ዓ.ም ጀምሮ በግንባታ ላይ የነበሩ 26 የተለያዩ የልማት ፕሮጀክቶች በዛሬው እለት ተመርቀዋል። ከ100 ሚሊየን ብር በላይ በሆነ ወጪ የተገነቡትን የልማት ፕሮጀክቶችም በምክትል ርእሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተሞች ዘርፍ አስተባባሪ ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ የተመራ የክልሉ መንግስት ልኡካን መርቀዋቸዋል። ግንባታቸው ተጠናቆ ከተመረቁ ፕሮጀክቶች ውስጥም ጌጠኛ ድንጋይ (ኮብል ስቶን) መንገዶች፣ የጠጠር መንገዶች የፍትህና የወረዳ ፍርድ ቤት ጽህፈት ቤቶች እና የመናፈሻ ስፋራዎች ይገኙበታል። በተጨማሪም ወይዘሮ ጫልቱ ሳኒ በክረምት በጎ ፍቃድ መርሃ ግብር በበጎ ፍቃደኞች የሚካሄድ በጅማ ከተማ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ውስጥ የተጨማሪ የመማሪያ ክፍሎች ግንባታ እንዲሁም ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው 98 ሰዎች የመኖሪያ ቤት ግንባታና እድሳትን መርሃ ግብርም አስጀምረዋል።የዜና ሰዓት ሳይጠብቁ የፋና ብሮድካስቲንግ ኮርፖሬትን ትኩስ እና ሰበር ዜናዎችን በፍጥነት በአጭር የፅሁፍ መልዕክት መልክ በስልክዎ ላይ እንዲደርስዎ ወደ 8111 OK ብለው ይላኩ። | 0 |
d36b73d397a407208f31f5eff790944d | c3ef9691a31cc01354385cf66697fc68 | ከፍተኛ ሊግ ምድብ ሀ ፡ መሪዎቹ ወልዋሎ እና መቐለ ከተማ ድል ሲያስመዝግቡ ባህር ዳር ከተማ ነጥብ ጥሏል | 09:00 የጀመሩ ጨዋታዎች ምድብ ሀFT መቐለ ከተማ 1-2 ወሎ ኮምቦልቻ (ውቅሮ)FT ሱሉልታ ከተማ 2-0 አክሱም ከተማ (ሱሉልታ)FT ፋሲል ከተማ 1-0 ወልድያ (ጎንደር)FT አዲስ አበባ ፖሊስ 0-2 አማራ ውሃ ስራ (አበበ ቢቂላ)FT ቡራዩ ከተማ 2-3 ኢትዮጵያ መድን (ቡራዩ) ምድብ ለFT ነቀምት ከተማ 0-0 ደቡብ ፖሊስ (ነቀምት)FT ጂንካ ከተማ 0-0 ጅማ ከተማ (ጅንካ)FT ባቱ ከተማ 1-2 ድሬዳዋ ፖሊስ (ባቱ)FT ሀላባ ከተማ 2-0 ነገሌ ቦረና (ሀላባ) 10:00 የጀመረ ጨዋታFT ናሽናል ሴሜንት 0-2 ወራቤ ከተማ (ድሬዳዋ) የትላንት ጨዋታ ውጤትፌዴራል ፖሊስ 0-1 አርሲ ነገሌ ማክሰኞ የሚደረጉ ጨዋታዎች09፡00 ሰበታ ከተማ ከ ወልዋሎ አዲግራት ዩኒቨርሲቲ (ሰበታ)09፡00 ኢትዮጵያ ውሃ ስፖርት ከ ሰሜን ሸዋ ደብረብርሃን (አበበ ቢቂላ) ለሌላ ጊዜ የተላለፉ ጨዋታዎችሙገር ሲሚንቶ ከ ባህርዳር ከተማጅማ አባ ቡና ከ አአ ዩኒቨርሰቲሻሸመኔ ከተማ ከ አዲስ አበባ ከተማ | 0 |
bebbab215c31953bd43747f57ad44d72 | e3e376ffb021dceb4c66168a3d54f11e | ትረምፕ በሜክሲኮ ፍልሰተኞች ጉዳይ | በዩናይትድ ስቴትስ ፖለቲካዊ ህይወት ውስጥ ንቁ ተሣታፊ ከሆኑ ትውልደ ኢትዮጵያ አሜሪካዊያን አንዱ የሆኑት አቶ ላባን የማነ የተመዘገቡ ሪፐብሊካንና የፕሬዚዳንት ትረምፕ ብርቱ ደጋፊ ናቸው።ከአቶ ላባን ጋር በወግ አጥባቂ ርዕዮት ምንነት፣ በዋሺንግተን ፖለቲካ፣ በጤናና በኮቪድ-19፣ በአካባቢ ጥበቃና በአየር ንብረት ለውጥ፣ ዘርና አሜሪካ በሚሉ ርዕሶችና በኅዳሴ ግድብ ጉዳይ ላይ ለፕሬዚዳንት ትረምፕ ካላቸው ድጋፍ ጋር እያያዙ አስተያየቶቻቸውን ሰጥተዋል።
| 0 |
6aa9afc4fc7de560386321583c4d2e5c | 9fdfb4503111c98e6b56576bab1e9362 | በኢትዮጵያ 24 ሰዓታት 653 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ ሲገኝባቸው፤ የ11 ሰዎች ሕይወት አልፏል | አዲስ አበባ ፣ ህዳር 2፣ 2013 (ኤፍ.ቢ.ሲ)ባለፉት 24 ሰዓታትም ውስጥ በተደረገው 5 ሺህ 181 የላብራቶሪ ምርመራ 400 ሰዎች የኮሮና ቫይረስ እንደተገኘባቸው የጤና ሚኒስቴር አስታውቋል።በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 100 ሺህ 727 መድረሱንም ሚኒስቴሩ ያወጣው እለታዊ መረጃ ያመለክታል።ከዚህ ባለፈ የ8 ሰዎች ህይወት በቫይረሱ ምክንያት ያለፈ ሲሆን፥ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ በቫይረሱ ምክንያት ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር 1 ሺህ 545መድረሱንም አመላክተዋል።በሌላ መልኩ በትናንትናው እለት 981 ሰዎች ከኮሮና ቫይረሱ ያገገሙ ሲሆን፥ በአጠቃላይ ከበሽታው ያገገሙ ሰዎች ቁጥር 62 ሺህ 497 መድረሱም ተገልጿል።ከቫይረሱ ጋር በተያያዘ እስካሁን ለ1 ሚሊየን 539 ሺህ 653 ሰዎች ምርመራ የተደረገ ሲሆን፥ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ቫይረሱ በምርመራ የተገኘባቸው ሰዎች ቁጥር 100 ሺህ 727 ደርሷል።አሁን ላይ ቫይረሱ ያለባቸው ሰዎች ቁጥር 36 ሺህ 683 ሲሆን፥ ከእነዚህም ውስጥ 292 ሰዎች በጽኑ የታመሙ መሆናቸውንም የጤና ሚኒስቴር መረጃ ያመለክታል። | 0 |
97050fa9f26879c61b18cef38cbe4c21 | b8d9790a65a302900142dfe441936e74 | አልማ በሦስት ወራት ውስጥ ሦስት ትምህርት ቤቶችን አስገንብቶ ለማኅበረሰቡ አስረከበ፡፡ በቀጣይ ሰፊ የለውጥ እቅድ ይዞ እየሠራ በመሆኑ የሕዝብ ተሳትፎው ተጠናክሮ እንዲቀጥልም ጥሪ አቅርቧል፡፡ | አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 26፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የገና በዓልን ምክንያት በማድረግ ለ120 ነዋሪዎች 25 ቤቶችን አስረከበ፡፡ቤቶቹን የአዲስ አበባ ከተማ ምክትል ከንቲባ ኢንጅነር ታከለ ኡማ ለ120 ነዋሪዎች የተገነቡትን 25 ቤቶችን አስረክበዋል፡፡ቤቶቹ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ልዩ ስሙ ጨርቆስ በሚባለው አከባቢ ለመኖር አስቸጋሪ በሆነ ሁኔታ ውስጥ ለነበሩ አቅመ ደካማ ነዋሪዎች ኮንትራክተሮችን በማስተባበር የተገነቡ ናቸው፡፡ኢንጂነር ታከለ ኡማ ቤቶቹን ባስረከቡበት ወቅት የከተማ አስተዳደሩ ለኑሮ ምቹ የሆኑ የመኖሪያ መንደሮችን በሁሉም የኑሮ ደረጃ ላይ ላሉ ነዋሪዎች የማቅረብ ስራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል፡፡ኢንጂነር ታከለ ቤቶቹን የገነቡ ኮንትራክተሮችን ያመሰገኑ ሲሆን ከሌሎች ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎች ጋር በመሆን መኖሪያ ቤቶቹን ጎብኝተዋል፡፡የመኖሪያ ቤቶቹ በቂ የንጹህ ውሃ አቅርቦትን ጨምሮ የመጸዳጃ ቤቶች እና የጋራ የማብሰያ ስፍራን ያካተተ መሆኑን ከአስተዳደሩ ከንቲባ ፅህፈት ቤት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡ | 0 |
0da016df3d170791c118679969f01a35 | e86f705f065db90494afb6d37dabbd66 | የኢትዮ ቴሌኮም 5 በመቶ ድርሻ ለኢትዮጵያ ዜጎች በአክስዮን እንደሚሸጥ ተገለፀ | የኢትዮ ቴሌኮም ምዕራብ ሪጅን ኦፕሬሽን ዳይሬክተር የሆኑት ገመቺስ ታደሰ በነቀምት ከተማ መገደላቸውን የአዲስ ማለዳ ምንጮች አረጋገጡ። የተቋሙ ዋና ስራ አስፈፃሚ ጽሕፈት ቤት ኃላፊ የሆኑት ጨረር አክሊሉ የዳይሬክተሩን ሕይወት ማለፉን ያረጋገጡ ሲሆን የአሟሟታቸውን ሁኔታ በመጣራት ላይ መሆኑን ለአዲስ ማለዳ ተናግረዋል። | 0 |
3d15fa3e783188530a6e8130c0704c2e | 69fe6a20266a901b07781ead9243bdf0 | በሊብያ ላይ ያተኮረ ዓለም አቀፍ የሚኒስትሮች ስብሰባ | ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ የደቡብ ኮሪያ ጉብኝታቸውን አጠናቀው ወደ ጃፓን አቅንተዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ የ42 አገራት መሪዎች በሚሳተፉበት የቲካድ የመሪዎች ስብሰባ ላይ ለመሳተፍ ነው ወደ ጃፓን ያቀኑት፡፡በዮኮሃማ ጃፓን ለሶስት ቀናት ለሚካሄደው የቲካድ የመሪዎች ስብሰባ በሚኒስትሮች ደረጃ የሚመክረው የአፍሪካ የሚኒስትሮች ጉባዔ ላይ የኢፌዴሪ የውጭ ጉዳይ ሚንስትር አቶ ገዱ አንዳርጋቸው የሚመራ ልዑክ እየተሳተፈ ይገኛል ፡፡በአፍሪካ ልማት ዙሪያ ምክክር የሚያደርገው የቶኪዮ አለም አቀፍ ኮንፈረንስ/ ቲካድ/ እ.አ.አ ከ1993 ጀምሮ አፍሪካ ከድህነት ለመውጣት የምታደርገውን ጥረት ለመደገፍ በጃፓን ጠንሳሽነትና አመራርነት የሚካሄድ ነው።በጥምር አዘጋጅነትም የአለም ባንክ፣ የተመድ ልማት ድርጅት እንዲሁም የአፍሪካ ህብረት ኮሚሽን እየተሳተፉ ይገኛል፡፡ | 0 |
a08151843606fcdd1d82226c9782b5c4 | 9bdacbb51eb268ba8e3b435aa0c92b2b | በኢትዮጵያዊያን ስለተዘጋጀው የአፍን አፍንጫ መሸፈኛ ፋሽን ትርኢት | አዲስ አበባ፣ ግንቦት 6፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግና የተጠሪ ተቋማት ሰራተኞች ከወር ደሞዛቸው በማዋጣት ለኮቭድ-19 መከላከል ስራ የ3 ሚሊየን ብር ድጋፍ አደረጉ።በተጨማሪም ካሁን በፊት በእርዳታ የተሰጠውን 21 ሺህ የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ ጭምብል፣ 160 የኬሚካል ምርጫ መሳሪያ እና 10 የሙቀት መለኪያ ቴርሞ ሜትር ድጋፍ አድርጓል።የአፍና አፍንጫ መሸፈኛ እና ኬሚካል መርጫዎቹ ለፌደራል ፖሊስ፣ ለአዲስ አበባ ፖሊስ እና ለፌደራል ማረሚየ ቤቶች አስተዳደር የሚሰጡ ናቸው ተብሏል።እንዲሁም 3 ሚሊየን ብሩ ደግሞ የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል ለተቋቋመው ለብሔራዊ ድጋፍ አሰባሰብ ኮሚቴ የሚሰጥ መሆኑም ነው የተገለፀው።የፌደራል ጠቅላይ አቃቤ ህግ ወይዘሮ አዳነች አቤቤም “ይህንን በመሰሉ የዜጎች መልካም ተግባርና የጋራ ርብርብ ወረርሽኙን ከሀገራችን በማጥፋት ታሪክ እንደምንሰራ አልጠራጠረም” ብለዋል በድጋፍ መስጠት ስነ ስርዓቱ ላይ።ድጋፉ ተልዕኳቸው የተሳካ እንዲሆን፣ እንዲያግዝና የቫይረሱን ስርጭት መቀነና መከላከል ላይ የጸጥታ ሃይሉ አረአያ እንዲሆን ለማድረግም ጭምር እንደሆነ ነው የጠቆሙት።የጸጥታ አካላት የቫይረሱን ስርጭትና የአስቸኳይ ግዜ አዋጁን ለማስፈጸም የሚያደርጉትን ርብርብ ስኬታማ እንዲሆን ህብረተሰቡ ለደንብና ለመመሪያ ተገዥ ሆኖ ሊያዛቸው ይገባልም ብለዋል።የብሔራዊ የድጋፍ አሰባሰብ ኮሚቴ የሃብት አሰባሰብ ንዑስ ኮሚቴ ሰብሳቢ አምባሳደር ምስጋኑ አረጋ ኮሮናቫይረስን ለመከላከልና ለመቆጣጠር በሚደረገው ርብርብ በርካታ ተቋማት፣ ባለኃብቶችና ግለሰቦች ድጋፍ እያደረጉ መሆኑን በማንሳት በተለይም ቫይረሱን ለመከላከል ግንባር ቀደም ሆነው ህዝብን ለሚያገለግሉ የጸጥታ አካላት መሆኑ የዛሬው ድጋፍ ለየት ያደርገዋል ብለዋል።በለይኩን ዓለም | 0 |
ecd2bef41d8577ed4d6f9cb4fafd2bd9 | 98ec0803d3567092dc541f69ae18864b | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ ጉዳይ ዛሬ ውሳኔ ያገኝ ይሆን ? | የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን አሰልጣኝ አብርሃም መብራቱ ከረዳቶቻቸው ጋር በመሆን በርካታ ታዳጊዎች ያቀፈው አዳማ እግር ኳስ ፕሮጀክት የተሰኘ ማሰልጠኛን ጎብኝተዋል፡፡በመላው ሀገሪቱ በመዞር የታዳጊዎችን የማሰልጠኛ ፕሮጀክቶችን በመጎብኘት፣ በማበረታታት እና በአንዳንድ ቦታዎች ላይ ደግሞ የቁሳቁስ ድጋፍን እያደረጉ የሚገኙት አሰልጣኝ አብርሀም መብራቱ አሁን ደግሞ ከኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጋር አዳማ የሚገኙ ሲሆን እግረ መንገዳቸውን እድሜያቸው ከ13-15 እና 17 ዓመት በታች በጥቅሉ ከ60 በላይ ተስፈኛ ወንድ እና ሴት ተጫዋቾችን አቅፎ በሚሰራው አዳማ የእግር ኳስ ማሰልጠኛ ፕሮጀክት ከረዳቶቻቸው ሙሉጌታ ምህረት፣ ፋሲል ተካልኝ እና ውብሸት ደሳለኝ ጋር በመሆን ዛሬ ከሰዓት በመመልከት ለሰልጣኞቹ ምክር እና ንግግር አድርገዋል፡፡አሰልጣኙ በንግግራቸው “የኢትዮጵያ የወደፊት የእግርኳስ ዕድገት በናንተው ልጆች እጅ ነው። ጠንክራችሁ በመስራት ለነገ ተተኪ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋቾች ትሆናላችሁ። ባላችሁ ነገር ላይ ቀጥሉ።” የሚል መልዕክት አስተላልፈዋል። አሰልጣኝ አብርሃም ለሶከር ኢትዮጵያ እንዳሉትም ለቀጣዮቹ ዓመታት በጊዜያዊ ውጤት ላይ ብቻ ማተኮር ሳይሆን በነዚህ ላይ በመስራት ቀጣይነት ያለው የጋራ ስራ በመስራት የማይቋረጥ ውጤት ለማምጣት ሁሉም የድርሻውን ይወጣ ብለዋል፡፡ | 0 |
2d18c847a9af8feddc4d456ca471bace | c61bbaeeb7732f2fce44cacc953074e0 | ‹‹የቤት ስራችንን በሜዳችን መጨረስ ይገባናል›› በሃይሉ አሰፋ | የ2010 የውድድር ዓመት የኢትዮጵያ ዋንጫ በዛሬው ዕለት ፍፃሜውን ሲያገኝ መከላከያ ቅዱስ ጊዮርጊስን በመለያ ምቶች 3-2 በማሸነፍ የዋንጫ ባለቤት ሆኗል። ባለፈው የውድድር ዓመት አጋማሽ ክለቡን በአሰልጣኝነት የተረከቡት ሥዩም ከበደም ከክለቡ ጋር የመጀመርያ ዋንጫቸውን አንስተዋል። አሰልጣኝ ሥዩም ከጨዋታው መጠናቀቅ በኋላ ለጋዜጠኞች የሰጡትን አሰለያየት እንዲህ አቅርበነዋል:-ስለ ውድድሩከነሐሴ 10 ጀምሮ ስንዘጋጅ የነበረው ለዚ ውድድር በማሰብ ነው። ምክንያቱም ይህ ትልቅ ውድድር ነው። ኢንተርናሽናል ውድድርን አስበን ነበር ዝግጅት ስንሰራ የቆየነው። ስለዚህ በስራነው ስራ ልክ ድሉ ይገባናል።ስለ ጨዋታው በመጀመሪያው አጋማሽ ከኋላ እስከ መሀል የነበረው እንቅስቃሴ ጥሩ ነበር፤ ፊት ላይ ትንሽ ይቀረን ነበር። ከዕረፍት መልስ ግን ያለብንን ችግር በመቅረፍ ጥሩ ተንቀሳቅሰናል። ጨዋታውን በ90 ደቂቃ ውስጥ መጨረስ የሚያስችሉ እድሎች ፈጥረን ነበር፤ ፈጣሪ ይመስገን የምንፈልገውን አግኝተናል።የኢትዮጵያ ዋንጫ ስኬትን በሊግ ላይ ስለመድገም የሊጉ ውድድር ላይ ትልቅ ጫና አለ። በአጥቂ በኩል በፍቃድ ላይ ያለው ፍፁም ገብረማርያም ሲመለስ ያለብንን ችግር እየቀረፍን እንመጣለን። በሲቲ ካፕ ውድድር ላይም ራሳችንን በደንብ እንፈትሻለን። በሊጉ የተሻሉ አጥቂ ስብስብ ያለው በአሁኑ ሳዓት መከላከያ ነው። ወደ ቡድኔ ከመጡት አዳዲስ 7 ተጨዋቾች መካከል በ6ቱ ተሳክቶልናል። ምክንያቱም ተጫዋቾቹ የመጡት ባለቡን ክፍት ቦታዎች ነው። ከአሰልጣኝ እስከ ተጫዋች በ2011 ታሪክ ለመስራት ትልቅ ተነሳሽነት ላይ በመሆናችን ሁላችንም ኃላፊነታችንን እንወጣለን። የኋላውን ታሪክ ጥለን በ2011 መከላከያ ለሻምፒዮንነት ነው የሚጫወተው። | 0 |
85176b0175e7cac65cf35acde5711a60 | 85176b0175e7cac65cf35acde5711a60 | ሙስሊም አሜሪካውያን ስለ ተመራጩ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ | ዶናልድ ትራምፕ ያን ሃሳብ ያቀረቡት ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ በርካታ የሽብር ጥቃቶች ከተካሄዱ በኋላ ነው።በስፋት ስጋት ለአደረበትና እምነት ለአጣው ሙስሊም አሜሪካዊ ማኅበረሠብ የዶናልድ ትራምፕ በፕሬዚዳንትነት መመረጥ ምን ማለት እንደሆነ ኬን ፋራቦ የዘገበችውን ሰሎሞን ክፍሌ ያቀርበዋል። ዝርዝር ዘገባውን ከተያያዘው የድምፅ ፋይል ያድምጡ። | 1 |
7ae47aa19c0cfd6c2d41dc05b405d886 | 675d9b67434b9b28ad3425a6486ce62e | የአዲስ አበባ ከተማ የሰላም ምክር ቤት ተመሰረተ | አዲስ አበባ ፣ ጥቅምት 10 ፣ 2013 (ኤፍ ቢ ሲ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክር ቤት 8ኛ አመት 1ኛ መደበኛ ጉባኤውን እያካሄደ ይገኛል። FacebookTwitterTelegramWhatsAppEmailViberPrintYou might also like የጥምቀት በዓል ተከበረ በአማራ ክልል የከተራና የጥምቀት በዓል ያለምንም ችግር መጠናቀቁ ተገለፀ የአዲስ አበባ ፖሊስ ኮሚሽን የከተራና የጥምቀት በዓል በሠላም መጠናቀቁን አስታወቀ አቶ ሙስጠፌ መሃመድ ከቆረሀይ ዞን የሀገር ሽማግሌዎች ጋር ተወያዩ Leave A Reply በብዛት የተነበቡ የክልል ርዕሳነ መስተዳድሮች ለብርሃነ ጥምቀቱ የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ ለጥምቀት በዓል የእንኳን አደረሳችሁ መልእክት አስተላለፉ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የሕወሃትን ህጋዊ ሰውነት መሰረዙን አስታወቀ በህገ ወጥ መልኩ ሲዘዋወር የነበረ ከ4 ሺህ 600 በላይ ተተኳሽ የክላሽ ጥይት ተያዘ 1 of 9 Facebook Twitter Google+ Youtube Instagram ክምችት | 0 |
b9738ff92de74953cb1d11188692e7a2 | d66eeec239851df7d2ff713d2830ea9f | የግብጽ ፍርድ ቤት በ28 ሰዎች ላይ የሞት ፍርድ አስተላለፈ | የግብጽ የጦር ሰራዊት ያሰረውን ጋዜጠኛና የሰብዓዊ መብት ተሟጋች ሆሳም ባጋትን፣ መንግስቱ በዛሬው ዕለት ነፃ ለቆታል።ጋዜጠኛው የተለቀቀው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት እና ኣንድ የሰባዓዊ መብት ተሙዋጋች ቡድን እስሩን ባወገዙት በማግስቱ መሆኑ ታውቋል።የግብጽ ባለስልጣናት ባጋትን ዕሁድ ዕለት ያሰሩት ሃያ ስድስት መኮንኖች መንግስት ልትገለብጡ ኣሲራችዋል ተብለው በጦር ፍርድ ቤት ተበይኖባቸዋል ብሎ ባለፈው ወር ባቀረበው ዘገባ የሃሰት ወሬ ኣሰራጭተሃል በማለት ወንጅለውት ነው።ባጋትን እጅግ ታዋቂ ከሆኑ የግብጽ የሰብዓዊ መብት ተሙዋጋቾች ኣንዱ ሲሆን የግብጽ መብቶች ተሙዋጋች ድርጅት የተባለው ቡድን መስራችም ነው።ጋዜጠኛው ጦር ፍርድ ቤት መቅረብ ይኖርበት እንደሆን ለጊዜው ኣናውቅም ብለዋል ጠበቃው። ጦር ሰራዊቱ ባጋትን የሀገር ብሔራዊ ደህንነት የሚጎዳ ተግባር ፈጽሙዋል፡ ሳይፈቀድለት ስለጦር ሃይሉ ጽሁፍ ኣውጥቷል ሲል ወንጅሎታል። | 0 |
f9ca58c55339c964126b9c65d48b134d | 8899bb73fa70ac934bd5b201d031046c | ማህበሩ ለካፒታል እቃዎች የሚውል 500 ሚሊዮን ብር መድቦ እየተንቀሳቀሰ ነው | የኦሮሚያ ልማት ማህበር (ኦልማ) ባለፉት 2 አመት ተኩል ጊዜ ከ717 ነጥብ 4 ሚሊዮን ብር በላይ ገቢ ማሰባሰቡን አስታወቀ፡፡ማህበሩ 10ኛ መደበኛ ጉባኤውን በአዳማ ከተማ አባ ገዳ አዳራሽ እያካሄደ ሲሆን፣ ማህበሩ የተመሰረተበትን 25ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ባለፉት ሁለት አመት ተኩል የተከናወኑ የስራ አፈፃፀም ሪፖርት ቀርቦ በተሳታፊዎች ውይይት እየተደረገበት ይገኛል፡፡በጉባኤው ንግግር ያደረጉት የቦርዱ ሰብሳቢ አቶ አባዱላ ገመዳ ልማት ማህበሩ ከ9ኛው ጉባኤ ወዲህ በትምህርት ዘርፍ ላይ ትኩረት ሰጥቶ በመስራት አመርቂ ውጤት ማስመዝገብ መቻሉን ገልጸው፣ በተለይም በአዳሪ ትምህርት ቤት በኩል ልዩ ተስጥኦ ያላቸውን ተማሪዎች አንድ ላይ በማስተማር የተሻለ ስራ ማከናወኑን ተናግረዋል፡፡በዚህም በትምህርት ጥራት በኩል ያስመዘገበው ለውጥ ለሌሎች አካባቢዎችም ተሞክሮ መሆን እንደሚችልም ጠቁመዋል፡፡“አንድነት ለልማት” በሚል መሪ ሐሳብ ባለፉት 2 አመት ተኩል በክልሉ ልማት ያገባኛል የሚሉ የተለያዩ አካላትን ከሀገር ውስጥም ሆነ ከውጭ በማሳተፍ መሰራቱ ተገልጿል፡፡ ከአባላቱም ከ300 ሚሊዮን ብር በላይ ለማሰባሰብ አቅዶ ከ284 ነጥብ 3 ሚሊዮን ብር በላይ ለመሰብሰብ መቻሉንም ታውቋል፡፡ከ25 ዓመታት በፊት በ1985 ዓ.ም. የተመሰረተው የኦሮሚያ ልማት ማህበር በአሁኑ ወቅት ከ6 ሚሊየን 700 ሺህ በላይ አባላት ያለው ሲሆን፣ በቆይታው ለክልሉ ህብረተሰብ ማህበራዊና ኢኮኖሚዊ ችግሮች መፍትሄ መሆን የቻሉ ከ1 ሺህ 700 በላይ ፕሮጀክቶችን ከ4 ቢሊዮን ብር በሚበልጥ ወጪ ገንብቶ ለአገልግሎት ማብቃት አንደቻለ በሪፖርቱ ተመልክቷል፡፡በጉባዔው ማጠቃለያ የቦርድ ሰብሳቢና አመራሮችን በመምረጥና በመሾም ይጠናቀቃል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ | 0 |
3f10208f9ced2e06cae873f30d2a0c45 | cb44ab8d34b416de08256f6bbbf4c5ee | ሣምንታዊ የስፖርት ፕሮግራም | አንጋፋው የአሜሪካዎቹና ካሪቢያን አህጉራዊ የእግር ኳስ ዋንጫ ውድድር ማለት ኮፓ አሜሪካ (COPA America)ዛሬ ማታ ዩናይትድ ስቴትስና ኮሎምቢያ ሳንታ ክላራ ካሊፎርንያ (Santa Clara, California) በሚያደርጉት ጨዋታ ይጀመራል። 16 ቲሞች የሚፋለሙበት ይህ ዓለምአቀፍ እግር ኳስ ዋንጫ ውድድር ዩናይትድ ስቴትስ ውስጥ ሲደረግ ለመደመሪያ ጊዜ ይሆናል። ኮፓ (COPA America)የተጀመረበትን 100ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ ዛሬ በሚጀመረው ጨዋታ፥ ጉዳት ደርሶባቸው ከቀሩ በጣት ከሚቆጠሩ የዓለም ዝነኛ ተጫዋቾች አብዛኞቹ ይገኛሉ ተብሏል።በቲም ደረጃም ባለፈው የዓለም ዋንጫ ለሩብ ፍጻሜው ከደረሱ ስምንቱ መካከል አራቱ ይሳተፋሉ። የስፖርት ፕሮግራም አዘጋጅና አቅራቢ ሰሎሞን ክፍሌ ይህ ታላቅ ውድድር ከመጀመሩ በፊት ተከታዩን ዘገባ አጠናቅሯል። | 0 |
End of preview. Expand
in Dataset Viewer.
README.md exists but content is empty.
- Downloads last month
- 56